UMMA TOKEN INVESTOR

Followings
0
No followings
Translation is not possible.

አላህ ሰዎችን በአንድ ጥፋት አያዋርድም። ለሰውም አያጋልጣቸውም። በዚያ ድርጊት ላይ የሚመላለስ ቢሆን እንጂ። ሁላችንም ወንጀል ሰርተናል። ብዙዎቻችን ወንጀላችን በእኛና በጌታችን አላህ(ሱወ) ዘንድ ነው። ሆኖም አላህ ይጠብቀንና ከመደጋገማችን ብዛት አላህን ረስተናል። የአላህ(ሱወ) ዝምታ አላህ የሌለ እስኪመስለን ድረስ ሆኗል። ቀልባችን ደርቋል። በወንጀል ላይ በየዕለቱ ስንዘወትር ብዙ የተውባ እድሎችን አበላሽተን በዱንያም በአኸራም ከመዋረድ አላህ ይጠብቀን! ወደርሱም ይመልሰን!

ድርጊቱ በኸሊፋው ዓሊ ኢብን አቢ ጣሊብ(ረዓ) ዘመን የተፈጸመ ነው። ሰውየው ሰርቆ ይያዝና እጁ እንዲቆረጥ ይፈረድበታል። እጁ ሊቆረጥ ሲል ያው የሌባ አይነደረቅ ነበርና "ያ አሚረል ሙዕሚኒን እኔኮ የመጀመሪያ ጊዜ መስረቄ ነው" ይላል። በዚህ ጊዜም አሊ ፈርጠም ብለው እንዲህ አሉት "አትዋሽ! የመጀመሪያ ስርቆትህ ቢሆን ኖሮ አላህ አያዋርድህም ነበር። ከዚህ በፊት የሰረቅከው ስርቆት ይኖራል" ሲሉት እጁ ሊቆረጥ የተዘጋጀው ሌባም ቀልቡ ደንገጥ ብሎ እንዲህ አለ፦ "ወላሂ እውነት ነው የተናገርከው! መቆረጤ ካልቀረማ እውነቱን ልናገር። አሁን የሰረቅኩት ለ21ኛ ጊዜ መስረቄ ነው" ብሎ አምኖ የሸሪዓው ህግ ሊፈጸምበት ችሏል።

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

•ከአመታት በፊት አንድ የሙስሊም ሀገር ላይ አንድ ሼኽ በሆነ መንደር ሲያልፉ የተወሰኑ ወጣቶች ቁማርና መሰል ሀራም ነገሮችን ሲፈፅሙ ይመለከቱና መጥፎ ነገር ሲሰራ ያየ በእጁ ይከላከል የሚለውን ሀዲስ ተግባራዊ ለማድረግ ሂደው የሚጫወቱበትን ብትንትን አድርገው አላህን እንዲፈሩና ከተግባራቸው እንዲቆጠቡ ተቆጥተው ይናገሯቸዋል።

ሼኹ በፈፀሙት ተግባር ስሜታቸውን መቆጣጠር ያቃታቸው ወጣቶች ሼኽዬውን ይደበድቧቸዋና እንሱ ጨዋታቸውን ይቀጥላሉ።

•በሌላ ቀን ሌላ ሼኽ በዚሁ መንደር በነዚህ ወጣቶች መሀል ያሀንኑ ሀራም ተግባር እየፈፀሙ ያልፋሉ።

እኚ ሼኽ መጥፎ ነገር ሲሰራ ያየ በእጁ ይከላከል የሚለውን ሀዲስ የተረዱበት መንገድ ከመጀመሪያው ፍፁም ይለያይ ነበር፣በመጀመሪያ ሄደው ለነዚህ ወጣቶች ከጥሩ ፈገግታ ጋ ኢስላማዊ ሰላምታን ያቀርቡላቸውና ያልፋሉ በሌላ ቀን ከሰላምታው በተጨማሪ በእጃቸው የሆነች ፍራፍሬ ነገር ይዘው ይመጡና ለሁሉም ይሰጧቸዋል፤በዚህ መልኩ የወጣቶቹን ልብ መግዛት የቻሉት እኚህ ሼኽ በሌላ ቀን መስጂድ የሆነ ፕሮጋራም እንዳለና ለመሄድ ፍቃደኛ ከሆኑ ይጠይቋቸዋል ብዙም ሳያንገራግሩ እሺ ብለው ይሄዳሉ፤መጠጥ ቤትና መሰል ሀራም ቦታዎች ይሄድ የነበረው እግራቸው አላህ እኚህን ሼኽ ሰበብ ያደርግላቸውና ወደ መስጂድ ይመላለስ ጀመር እነዚህ ሸባቦች በጊዜ ሂደት ተለውጠው የመስጂድ ሰው ለመሆን በቁ።ሀዲሱን በጥሬው ተረድተው ሂክማ ያነሳቸው(ደብድበዋቸው) የነበሩትን ሼኽ ሂደው አውፍ እንዲሏቸው ይጠይቃሉ።

~~~~~~~~~~~~~

Send as a message
Share on my page
Share in the group
jemal abdela Сhanged his profile picture
7 month
Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group