UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.

አንድ ሠው ሶቅራጠስ ወዳረፈበት እልፍኝ ይሄድና እንዲህ ይለዋል፡፡

‹‹ሶቅራጠስ ወዳጄ፣ ስለአንድ ጓደኛህ የሠማሁት ነገር ምንም ደስ አይልም፡፡››

ሶቅራጦስ መልስ ለመስጠት አልፈለገም፡፡ መከዳው ላይ ደገፍ እንዳለ በዝምታ ቆየ፡፡

---------------------------

ሠውየውም እንደገና ‹‹ይገርማል ከእርሱ አይጠበቅም፤ በጣም ገርሞኛል›› ሲል ተናገረ፡፡

ሶቅራጦስ፣ ይህ ሠው በቀላሉ እንደማይለቀው ስለተረዳ አንድ መደራደሪያ አቀረበለት፡፡

---------------------------

‹‹ስለ ወዳጄ ልትነግረኝ የፈለግከውን እንድሠማህ ከፈለግህ ሦስት ጥያቄዎች አሉኝ፤ እነርሱን በቅድሚያ ልትመልስልኝ ይገባል!

ይህ ሲሆን ብቻ ነው የምሰማህ። ›› አለው፡፡

ሠውየው ለወሬው ቢቸኩልም አማራጭ ስላልነበረው በሶቅራጠስ ሀሳብ ተስማማ፡፡

---------------------------

‹‹የመጀመሪያው ጥያቄዬ የእውነት ጥያቄ ነው" አለ ሶቅራጠስ።

"ስለወዳጄ የሠማኸው መቶ በመቶ እውነት ነው ወይ?›› ሲል ጠየቀ፡፡

ሠውየውም፡- ‹‹መቶ በመቶ እንኳን እርግጠኛ መሆን አልችልም›› ሲል እያመነታ መለሰለት፡፡

‹‹በጣም ጥሩ! ልትነግረኝ የፈለግከው እርግጠኛ ያልሆነ ነገር ነው ማለት ነው፡፡

---------------------------

እሺ ሁለተኛው ጥያቄዬ የመልካምነት ነው፡፡

የምትነግረኝ መልካም ነገር ነው ወይ?›› ሲል ሶቅራጠስ ጥያቄውን አቀረበ፡፡

ሠውየውም፡- ‹‹እርሱማ መልካም አይደለም›› አለ ቱግ ብሎ፡፡

የሶቅራጠስ ጥያቄዎች ለማውራት የቋመጠለትን ወሬ እንዳያወራ እንቅፋት መስለው ታዩት።

ሶቅራጦስም ‹‹እውነትነቱ ያልተረጋገጠና መልካም ያልሆነ ነገር ልትነግረኝ ፈልገሃል፡፡

---------------------------

እሺ ሶስተኛውና የመጨረሻው ጥያቄዬን ልጠይቅህ?›› አለው፡፡

ሠውየውም ጥያቄውን ለመስማት ፈጥኖ ‹‹እሺ›› አለ፡፡

ሶቅራጦስ ጠየቀ፤ ‹‹የምትነግረኝ ነገር ለእኔ የሚጠቅመኝ ነገር አለው ወይ?››

‹‹የለም! የለም! መጥቀም እንኳን አይጠቅምህም። ብቻ ብትሰማኝ...›› ብሎ ሰውዬው መቅለስለስ ጀመረ።

---------------------------

ይሄን ጊዜ ሶቅራጦስ ‹‹ታዲያ እውነትነቱ ያልተረጋገጠ፤ መልካም ያልሆነ እና ለእኔ ምንም ጥቅም የሌለው ነገር ልንገርህ ስትለኝ እንዴት እሰማሃለሁ። ዞር በል ካጠገቤ አልሰማህም!!›› አለው ይባላል፡፡

---------------------------

ስንቶቻችን ነን ሰው የሚነግረን ነገር እውነት፣ መልካምና ጠቃሚ መሆኑን አጣርተን የምንሰማው?

ስንቶቻችን ነን ለሰው ቁምነገር ብለን ልንናገር ስንል ከሶስቱ አንዱን ማሟላቱን የምናረጋገጠው?

አሁን እኮ ሰው ዝም ብሎ የተነገረውን ስለሚሰማ በቀላሉ እንደ እንስሳ የሚነዳ ሆኗል፡፡

በየሶሻል ሚዲያው ላይ ፖስት የሚደረጉት ብዙዎቹ መረጃዎች እውነት ያልሆኑ፣ መልካምነት የሌላቸው እና ለእኛ ምንም ጥቅም የማይሰጡ ናቸው፡፡

በተቃራኒው የውሸት መረጃዎች ሆነው ስንቱን ያጭበረበሩ፣ ሰይጣናዊ ርምጃ ለመውሰድ የሚገፋፉ ሆነው ሳለ ያለማቅማማት እንሰማቸዋለን፡፡

---------------------------

አሁን አሁን እውነት ከሚናገሩት ሰዎች በላይ በመርዝ የተለወሰ ውሸት የሚናገሩ ሰዎች የተሻለ ብዙ ተከታይ አላቸው፡፡

መልካም መልካሙን ከሚሰብኩ ሰዎች ይልቅ የጥፋት ሰባኪዎች ብዙ ደጋፊ አላቸው፡፡ ፍለጠው/ቁረጠው ባዮች ናቸው የጀገኑት፡፡

---------------------------

እነሱን ማስቆም አይቻል ይሆናል፤ ነገር ግን እነሱን አለመስማት/አለመከተል ቀላል ነው፡፡

እነዚህን የሶቅራጠስ 3ቱ ጥያቄዎችን እንደ ወንፊት ተጠቅመን ማጣራት ብቻ በቂ ነው፡፡

---------------------------

‹ፅሁፉን› እውነት፣ መልካም እና ጠቃሚ ሆኖ ካገኛችሁት ይህን ገፅ #follow በማድረግ ተከተሉን።

ሌሎችም ይማሩበት ዘንድ ይህን መልእክት #like #share አድርጉት፡፡ 🙏🙏🙏

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

የፍልስጤም ነፃነት ከሶርያ ጋር የተያያዘ ነው። ፍልስጤም ነፃ የምትወጣው ሶርያ ነፃ ስትወጣ ነው። ነቢዩ (ዐሰወ) በመጨረሻው ዘመን ሶርያ ዳቢቅ ላይ ከመስቀለኞች ጋር ጦርነት እንደሚደረግና ሙስሊሞችም አሸንፈው ሻምንና የተቀረውን ዓለም እንደሚከፍቱ እንዲህ ተናግረዋል፡-

«ሮማውያን አል-ዓማቅ ወይም ዳቢቅ ላይ ሳይዘምቱባችሁ በፊት ቂያማህ አትቆምም። በዚያን ጊዜ የዓለም ምርጥ የሚባሉት ህዝቦች ከመዲና ሊገጥሟቸው ይወጡና ከባድ ጦርነት ይጀመራል። በውጊያውም መሀል ከሙስሊሞች አንድ ሶስተኛው ይሸሻሉ። አንድ ሶስተኛው ሸሂድ ይሆናሉ። ቀሪዎቹ አንድ ሶስተኛው ደግሞ ያሸንፋሉ። ከዚያም ሸይጧን ይነሳና ደጃል አገራችሁንና ቤተሰቦቻችሁን ይዞባችኋል! ይላቸዋል። በዚህ ጊዜ ወደ አገራቸው ይመለሳሉ። ነገርግን የተባለው ውሸት ሆኖ ያገኙታል። ከዚያም ለሁለተኛ ጦርነት ወደ ሻም ሲመጡ ደጃል ይወጣልና ይከባቸዋል። በዚህ ጊዜ ዒሳ ኢብኑ መርየም ይወርድና መሪያቸው ይሆናል። የአላህም ጠላቶች ፊትለፊት በተገናኙት ጊዜ እንደ ጨው ይቀልጣሉ። ዒሳም በጦሩ ጫፍ ላይ ደማቸውን ለምልክት ያሳያቸዋል።»

(ሙስሊም፥ 2897)

ይህ የመጨረሻው ጦርነት እስኪፈፀም ደግሞ በሻምና በፍልስጤም ዙርያ በእምነታቸው ፀንተው የሚታገሉ ይኖራሉ። ነቢዩ (ዐሰወ) ስለነዚህ ቡድኖች ሲናገሩ እንዲህ አሉ፡-

‹‹ከሕዝቦቼ የተወሰኑ ቡድኖች በኃይማኖታቸው ፀንተው ይቆያሉ። ጠላቶቻቸውንም ያሸንፋሉ። የተቃወማቸው አይጎዳቸውም። በርግጥ መከራና ችግር ያገኛቸዋል። በዚህ ሁኔታ ላይ እያሉ የአላህ ውሳኔ (እርዳታ) ይፈፀማል።›› አሉ። ሰሃባዎችም ‹‹የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! እነኝህ ኃይላት የት ይገኛሉ?›› በማለት ጠየቋቸው። ነቢዩም (ዐሰወ) ‹‹በበይተል መቅዲስ (ቁዱስ) እና በዙሪያዋ›› በማለት መለሱ።››

(አህመድ)

ኢብኑ ተይሚያህ ‹‹እነዚህ ቡድኖች እንደማንኛውም ‹ሙስሊም› ብቻ የሚባሉ ሳይሆኑ ትክክለኛውን መንገድ አጥብቀው የያዙና የአላህ ውሳኔ እስኪመጣ ድረስ ፀንተው የሚቆዩ ናቸው።›› ብለዋል።

አላህ የድል መክፈቻውን ቀን ቅርብ ያድርገው

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

subhanallah

የጋዛ ከተማ ነዋሪ ለሙስሊም ሀገራት ያስተላለፈው መልእክት

"ሰላተል ጋኢብ ለመስገድ አትነሱ። እኛ በህይወት አለን የሞታችሁት እናንተ ናችሁ" 💔

Mahi

#ኡማ ላይፍ

😡🇮🇱👹

#freepalestinehomeland

#free_palestine

#አል_አቅሷ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ما شاء الله ♥

1 view
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

በጦር ሜዳ በተሰዋው የቀሳም ሙጃሂድ ኪስ ውስጥ የተገኘ ደብዳቤ። የወራሪዋ ጦር መሪ ለወታደሮቹ እያሳየ ደብዳቤው እንዲህ ይላል:-

"በኸይበር ጌታ በአላህ ስም እንጀምራለን

በዙልፊቀርም ሰይፍ ሰንዝረን እንመታለን።

ወራሪዋ ጠላትህ ናት። ልክ እንደ በሽታ። ግንባር ደረቱን ልብና ጉበቱ ላይ አነጣጥረህ ከመምታት በቀር ምንም ዓይነት መድኃኒት የሌለው በሽታ መሆኑን እወቅ። አጥፋቸው የአቡ ሱለይማንን የኻሊድን ሰይፍ ተጠቅመህ ሰንዝርባቸው"

በኸይበር ጌታ በአላህ ስም እንጀምራለን

በዙልፊቀርም ሰይፍ ሰንዝረን እንመታለን

Send as a message
Share on my page
Share in the group