UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.

ጋአዛን በተክቢራ ዉቦቹ ሲያደምቋት

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

የፋኖ ትግል የሃይማኖት ነው

~

ወደ ዋናው ነጥብ ከመግባቴ በፊት ትላንት ከመግሪብ ሶላት መልስ የተገደሉት ወንድሞቻችን 3 እንደሆኑ ገልጬ ነበር። ኋላ ላይ በደረሰኝ መረጃ ግን ሟቾቹ አምስት ናቸው። ሙሔ ሰሜ፣ አበባው ሙሄ፣ ሙሉ ሀብት ሙሄ፣ ብርሀኑ ሙሄ እና ኢድሪስ መኮነን ናቸው። አላህ ሸሂድነትን ይወፍቃቸው።

ወደ ነጥቤ ስመለስ የዚህ ገዳይ ስብስብ አላማ ሃይማኖት ተኮር ነው። ተወደደም ተጠላም እውነታው ከዚህ የራቀ አይደለም። መሬት ላይ ያለ ተጨባጭ በሸንጋይ ቃላት አይሸፈንም። አላማቸው ሃይማኖት እንደሆነ የሚያሳዩ ብዙ ምክንያቶች አሉ። የተወሰኑትን እንይ፦

1ኛ፦ ፋኖዎች በተደጋጋሚ ትግላቸው ለማተባቸው እንደሆነ ገልፀዋል። ይሄ ግልፅ መልእክት የያዘ ነው።

2ኛ፦ በተደጋጋሚ ጠቅላይ ሚኒስትሩን በሙስሊምነት መክሰሳቸውም የልጅ እያሱን ዘመን ያስታውሰናል። ልጅ እያሱ በሙስሊምነት ተከስሶ ነው ከመንበሩ የተፈነገለው። ሙስሊምነት ለቤተ መንግስት የማያበቃ ወንጀል ነው። ይሄ ክሳቸው ለሙስሊሞች ምን አይነት እይታ እንዳላቸው፣ ምናባቸው ውስጥ ባለችው ኢትዮጵያ ውስጥ ሙስሊሞች ምን አይነት ቦታ እንዳላቸው የሚጠቁም ነው።

3ኛ፦ በተደጋጋሚ የፋኖ ደጋፊ ቄሶች በቲቪ ቀርበው ከግራኝ ዘመን የከፋ ጊዜ ላይ ነው ያለነው ሲሉ ነበር። ይህም ራሱ ደረሰብን የሚሉትን ጭቆና ከእምነት ጋር እያያያዙትና ከሙስሊሞች ጋርም እያነካኩት እንደሆነ ነው የሚያሳየው።

4ኛ፦ በተደጋጋሚ ሙስሊሞችን ለይተው እያጠቁ ነው። በርካቶች ተገድለዋል። በርካቶች የትውልድ ቀያቸውን ጥለው ሸሽተዋል። በርካቶች እየታገቱ የተጋነነ ገንዘብ እየተጠየቁ የቻሉ ከፍለው ሲወጡ ያልቻሉ ተገድለዋል። አንዳንዶቹ የተጠየቁትን ገንዘብ ከፍለውም አልተለቀቁም። ሰሜን ሸዋ ላይ አንድ ሙስሊም ባለሃብት ታግቶ ሶስት ጊዜ ጠመንጃ አስገዝተውታል። ሆኖም ግን እስከ ቅርብ ጊዜ ባለኝ መረጃ አልለቀቁትም። አሁን ደግሞ እገታው መልኩን ቀይሮ ሌሊት ላይ በቡድን ሆነው እየመጡ በር እየሰበሩ ነው እያገቱ ያሉት።

5ኛ፦ በተደጋጋሚ መስጂዶች ላይ ጥቃት እየፈፀሙ ነው።

6ኛ፦ ይህ ሁሉ ሲሆንም ቡድኑና ደጋፊዎቹ ለይስሙላ ያክል እንኳ በሙስሊሞች ላይ የሚደርሰውን የተናጠል ጥቃት አምነው ሲያወግዙ አይሰሙም። ይህን ከማድረግ ይልቅ ሽምጥጥ አድርገው መካድን የሙጥኝ ብለዋል። አሁን አሁን መረጃዎች እየበዙ ሲመጡ ደግሞ መንግስት ነው አውቆ ሙስሊሞችን እየገደለ ልዩነት ለመፍጠር የሚሰራው እያሉ ነው። ይሄ አይን ያወጣ ቅጥፈት ነው። ብዙ ቦታ ላይ በስም ተለይተው የሚታወቁ ፋኖዎች ጭምር ናቸው ጥቃቱን እየፈፀሙ ያሉት። የመንግስት ጥፋት እነዚህ አረመኔዎች ላይ በቂ እርምጃ አለመውሰዱ ነው።

7ኛ፦ በተደጋጋሚ “ነባሩ እስልምና” እና “ወሃብያ” እያሉ በሙስሊሙ የውስጥ ጉዳይ ገብተው እያቦኩ ነው። በተደጋጋሚ ልክ ለኢስላምና ለሙስሊሞች የሚቆረቆሩ ይመስል “ነባሩ እስልምና ተገፋ" እያሉ ለአሕባሽ ውግንናቸውን እያሳዩ ነው። ይህን የሚያደርጉት ለሁለት አላማ ነው። አንድም በዘር ትብታብ የተጠለፉ ሙስሊሞችን ለማደንዘዝ ነው። ሁለትም ሙስሊሞችን ለማጥቃት የአሕባሽ ቡድን ጥሩ አጋር ስለሚሆናቸው ነው።

8ኛ፦ ጊዜያዊውን መጅሊስ የብልፅግና መንግስት ደጋፊ ነው በሚል ማመሃኛ በመጅሊሱ መዋቅር ውስጥ የገቡ ሙስሊሞችን እስከመግደል ደርሰዋል።

9ኛ፦ ሰሜን ሸዋ ላይ አርጎባዎችን አብራችሁን ካልተሰለፋችሁ በሚል ተደጋጋሚ ዛቻዎችንና ትንኮሳዎችን ፈፅመዋል። ስለ ምክንያቶቹ ዝርዝር ማጣራት የሚሹ ቢሆኑም የተፈፀሙ ግድያዎችም አሉ።

10ኛ፦ ቤተ ክርስቲያናትና ገዳማትን የመሳሪያ ማከማቻና የጥቃት ማቀነባበሪያ ማዕከላት ካደረጉ በጣም ቆይተዋል።

ይህን ሁሉ እያደረገም “ወለጋ ላይ አማራ ሙስሊሞች በብሄራቸው ሰበብ ሲገደሉ የት ነበራችሁ?” የሚል ቁማር እየተጫወተ ነው። ቁማሩ ሰርቶለት አንዳንድ በዘር ትብታብ የተተበተቡ ሞኞችን ጠልፎለታል።

1ኛ፦ ብሄር እያዩ በሬሳ ቁማር መስራት የፖለቲከኛ ስራ ነው። ኦሮሞ ሆኑ አማራ ወይም ሌላ፡ ዘር እያዩ ጥላቻና ውግንና ከሚያሳዩት ጋር ይህን ብትሉ ልክም ባይሆን የሆነ ያክል ስሜት ይሰጥ ነበር። ትላንት ስንጮህ ለነበርነው ግን ይህን ማለት አትችሉም።

2ኛ፦ የወለጋውን ኬዝ የምታነሱትም ለማታገያነት ስለሚጠቅማችሁ እንጂ ለሰለባዎቹ ተቆርቁራችሁ አይደለም። ብትቆረቆሩማ በብሄር የሚመስሏችሁን አካላት በእምነት እየለያችሁ ባላጠቃችሁ ነበር።

3ኛ፦ ሂሳባችሁ የጅል ሂሳብ ነው። ኦሮሚያ ውስጥ ሲገደሉ ዝም ስላላችሁ አማራ ውስጥ ስንገድልም አትናገሩን ነው እያላችሁ ያላችሁት። ይህም ብልጠት ሆኖ ሰው ሲሸውድ አስቡት እንግዲህ።

የሚደንቀው በእንዲህ አይነት ጅላጅል ብልጠታቸው የጠለፉት ሙስሊም መኖሩ ነው። በነገራችን ላይ እነዚህን አካላት እየደገፉ ያሉ ሙስሊሞች 3 አይነት ናቸው።

1ኛው፦ በመጅሊስ ጉዳይ ያኮረፈ አሕባሽ ነው። እነዚህ በማህበራዊ ሚዲያ ብቻ አይደለም ለፋኖ እየታገሉ ያሉት። ይልቁንም ጫካ ጭምር ገብተው አብረው የተሰለፉ አሉ። በአንዳንድ ቦታዎች ሙስሊሞች ላይ ከሚደርሱ ጥቃቶች ጀርባ የእነዚህ አካላት ጥቆማና ተሳትፎ አለ።

2ኛው ክፍል ምክንያቱ ብሄር ወለድ ቅራኔ ነው። የመንግስትን ፖለቲካ፣ ኦሮሚያ ላይ የደረሱ ዘር ተኮር ጥቃቶችን እንደ ግብአት ይጠቀማል። ይሄ ክፍል በክልሉ ውስጥ ሙስሊሞች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን እያወቀ አንዴ መንግስት ነው፣ አንዴ ውሸት ነው እያለ ራሱን የሚያታልል ነው። ውጭ ሃገር ሆነው የገንዘብ ድጋፍ የሚያደርጉትም ብዙዎቹ በዚህ ምድብ ስር የሚካተቱ ናቸው።

3ኛው ክፍል፦ በተለያዩ የአስተዳደር ችግሮች መነሻ በክልሉ ውስጥ ወይም በታችኛው የመንግስት መዋቅር ላይ ያቄመ አካል ነው። ነገሮችን አርቆ የሚመለከትበት በቂ ንቃት የለውም። የሌሎችን ጩኸት ከማስተጋባት ባለፈ የረባ የተዋቀረ ሃሳብም የለውም። ጉዞው እንዲሁ የደመነፍስ ነው።

ለጊዜው እዚህ ላይ ላቁም። ምናልባት በቀሪ ሃሳቦች ላይ ልመለስ እችላለሁ።

=

የቴሌግራም ቻናል :-

https://t.me/IbnuMunewor

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

የለተሞ ጉዶች ምንአየሰሩ ነዉ ??

ሽርክን ቢድዓን የሚያወግዙ ኪታቦች ተቃጠሉ ቢባል  ወይም   ሱናንና የሱና መሻይኾች የሚያወሱ  ኩቱቦቾ  ጠቃጠሉ መባልን ብትሰማ    ይህን  ግፍ የፈጸመዉ  ማን  ሊሆን ይችላል ብትባል     ግምትህ  ማን ይሆናል ??  አህባሽወይም ሶፍያ??  ምነዉ  እነሱ በሆኑና ቢያንስ በወጉ ባዘን ነበር።

ነገሩ  ወዲህ ነዉ   ምቀኝነትና  ቡድንተኝነት  አቅላቸዉን ያሳተቸዉ የለተሞ መንጋ  ሙሪድነታቸዉን  የሱና ኩቱቦችን በማቃጠል መግለጽ ጀምረዋል።     ድንበር ማለፍ መጨረሻሁ ይህቢሆን አይግረምምህ።

ስለ ተዉሒድና ሱና የሚያስተምሩ መጽሐፍትን  ማቃጠል  በየትኛዉ  ሂሳብ ተሰልቶ ነዉ  ዲንንመርዳት የሚሆ ነዉ??

ምነዉ ታድያ  እስከዛሬ ይህን ተግባራቸዉን  በ አህባሽ ወይም በ አሻዒራና ማቱሩዲይ  ኩቶቦችላይ    አልፈጸሙም   ያዉም የ አህባሾች    መጸሀፍ ሙሉ ለሙሉ የሽርክ የተሰዉፍና የቢድዓ መጽሐፍ ሆኖሳለ???

ይግረማቹ   አምዋትን  መጣራት  ዶሪህን ማምለክ  ይበቃል የሚሉ መጸሀፍት በ ክብር አስቀምጠዉ    ይህንን ጥመትን የሚዋጋና ወደ ተዉሂድ ወደ ሱና የሚጣሩ መጽሐፍትን ማቃጠል ምንይሉታል   ???

ያዉም ይን ተገባር የሚተገብረዉ  እራሱን የጠራ የተጥራራ የሱና ሰዉ  ነኝ ብሎ የሚሞግት አካልሲሆን  አስቡት  ???

ይህ ዓይንህን ጨፍንና ላሞኝህማለት አይሆንም?

በቁጭታችሁ ሙቱ እንላቸዋለን መችም  ሀቅ የበላይመሆኑ አይቀሬነዉ

አላህ ዲንን ያለአግባብ ከማጥበቅም ሆና ቀመዝቀጥ ይጠብቀን!!!!

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

የለተሞ ጉዶች ምንአየሰሩ ነዉ ??

ሽርክን ቢድዓን የሚያወግዙ ኪታቦች ተቃጠሉ ቢባል  ወይም   ሱናንና የሱና መሻይኾች የሚያወሱ  ኩቱቦቾ  ጠቃጠሉ መባልን ብትሰማ    ይህን  ግፍ የፈጸመዉ  ማን  ሊሆን ይችላል ?   

አህባሽወይም ሶፍያ??  ምነዉ  እነሱ በሆኑና ቢያንስ በወጉ ባዘን ነበር።

ነገሩ  ወዲህ ነዉ   ምቀኝነትና  ቡድንተኝነት  አቅላቸዉን ያሳተቸዉ የለተሞ መንጋ  ሙሪድነታቸዉን  የሱና ኩቱቦችን በማቃጠል መግለጽ ጀምረዋል ድንበር ማለፍ መጨረሻሁ ይህቢሆን አይግረምምህ።

ስለ ተዉሒድና ሱና የሚያስተምሩ መጽሐፍትን  ማቃጠል  በየትኛዉ  ሂሳብ ተሰልቶ ነዉ  ዲንንመርዳት የሚሆ ነዉ??

ምነዉ ታድያ  እስከዛሬ ይህን ተግባራቸዉን  በ አህባሽ ወይም በ አሻዒራና ማቱሩዲይ  ኩቶቦችላይ    አልፈጸሙም   ያዉም የ አህባሾች    መጸሀፍ ሙሉ ለሙሉ የሽርክ የተሰዉፍና የቢድዓ መጽሐፍ ሆኖሳለ???

ይግረማቹ   አምዋትን  መጣራት  ዶሪህን ማምለክ  ይበቃል የሚሉ መጸሀፍት በ ክብር አስቀምጠዉ    ይህንን ጥመትን የሚዋጋና ወደ ተዉሂድ ወደ ሱና የሚጣሩ መጽሐፍትን ማቃጠል ምንይሉታል   ???

ያዉም ይን ተገባር የሚተገብረዉ  እራሱን የጠራ የተጥራራ የሱና ሰዉ  ነኝ ብሎ የሚሞግት አካልሲሆን  አስቡት  ???

ይህ ዓይንህን ጨፍንና ላሞኝህማለት አይሆንም?

በቁጭታችሁ ሙቱ እንላቸዋለን መችም  ሀቅ የበላይመሆኑ አይቀሬነዉ

አላህ ዲንን ያለአግባብ ከማጥበቅም ሆና ቀመዝቀጥ ይጠብቀን!!!!

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group