UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ሱብሀን አላህ💔

11 views
1 view
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

የእስራኤል የእብደት ጥግ‼

===================

✍ ተመድ ተብዬውና መሰል ጥርስ የሌላቸው አንበሶች ዝም ስላሏት፤ በጋዛ ከተማ ንጹሐን ላይ ሆስፒታልና የስደተኞች መጠለያ ካምፕ ሳይቀር 24/7 እያዘነበችው ያለው ቦምብ አላረካት ብሎ ዛሬ የቅርስ ሚኒስተሯ እንዳሳወቀው ከሆነ ኒዩክሌር (አቶሚክ ቦምብ) ሊጠቀሙ እንደሚችሉ አሳውቋል።

በርግጥ ጠቅላይ ሚኒስተሯን ጨምሮ ሌሎችም ኃላፊዎች ይህንን የጓደኛቸውን ንግግር ለማውገዝ ሞክረዋል። ግን ምናልባትም ሚስጥር ለምን አወጣ ብለው ይሆናል እንጂ ውስጣቸው አይፈልገውም ማለት አይቻልም። ምክንያቱም አሁን እየሄዱበት ባለው ጭፍጨፋ ካልረኩና የፈለጉትን ካላሳኩ አቶሚክ ቦምብ ላለመጠቀማቸው ዋስትና የለም።

በርግጥ እስካሁን ያዘነቡትም ቦምብ ሁለት አቶሚክ ቦምብ እንደሚገመት ተነግሯል።

ስለ አቶሚክ ቦምብ ለማታውቁ አሜሪካ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት ኦገስት 6, 1945  በጃፓኗ ሒሮሽማ ከተማ ላይ፣ ከ3 ቀን በኋላ ደግሞ ናጋሳኪ ከተማ ላይ በጣለችው አቶሚክ ቦምብ እስከ 226,000 የሚጠጋ ህዝብ ነበር የጨረሰችው። እጅግ በጣም አውዳሚ መሳሪያ ነው።

እስራኤል በሰሜን ጋዛ አንድም መኖሪያ ቤት መኖር የለበትም ብላለች። የቀሩት ነዋሪዎችም ወደ ደቡብ ጋዛ ይሂዱ ብላለች። ግን መንገድ ላይና እዛው ደቡብ ጋዛ ላይም ማውደሟን ቀጥላለች።

ዓለም አሁንም ዝምታውን ቀጥሏል። ይህቺን እብድ ውሻ ማሰር አልቻለም።

አላህ በራሷ አቶሚክ ቦምብ ራሷን ያፈንዳትና ይገላግለን።

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

😭😭😭

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

የዓለም ህዝብ ግን አይገርምም⁉️

=======================

(ዓለም በዚህ ዘመን አይታው የማታውቀው የጦር ወንጀልና የዘር ጭፍጨፋ በጘዝ'ዛ)

||

✍ 365 km² ስፋት ባላት አነስተኛ ከተማ ውስጥ 2.3+ ሚሊዮን ዜጎች ተጠጋግተው ይኖሩባታል። በዚህች densely populated በሆነች ከተማ ላይ ለተከታታይ 3 ሳምንታት ያላባራ ከ12 ሺህ ቶን በላይ ቦምብ ሲዘንብ፤ በዚህም ሳቢያ፦

1) በትንሹ 7,028 የሚሆኑ ፈለስጢናዊ ሙስሊሞች ሲገደሉ፣

2) ከ70% በላይ የሚሆኑት ህፃናትና ሴቶች ሲሆኑ (2,913 ህፃናትና 1,709 ሴቶች)፣

3) 18,482 የሚሆኑት ለከፍተኛ የአካል ጉዳት ሲዳረጉ፣

4) ባለፉት 24 ሰዓታት ብቻ 481 የሚሆኑት ሲገደሉ (ከመካከላቸው 209 የሚሆኑት ህፃናት ናቸው።)፣

5) ከ1,650 በላይ የሚሆኑት ጀናዛቸው እንኳ ሳይገኝ እስካሁን ድረስ በቦምብ በፈራረሱት ህንፃዎች ስር ሲሆኑ (ከመካከላቸው 940 ህፃናት አሉበት።)፣

6) 731 የሚሆኑ ፈለስጢናዊ ሙሉ ቤተሰቦች ሲገደሉ፣

⑦) 101 የጤና ባለሙያዎች ሲገደሉና 100 የሚሆኑት ሲቆስሉ፣

⑧) 12 ሆስፒታሎችና 32 የጤና ማዕከላት በነዳጅ እጥረትና በቦምብ ጥቃት ከአገልግሎት ውጭ ሲሆኑ፣

9) በኢንኩቤተር ውስጥ የሚገኙ ከ130 በላይ የሚሆኑ ህፃናት ያሉበት ሆስፒታል ባጋጠመው በነዳጅ እጥረት ሳቢያ ነፍሳቸው በእንጥልጥል ላይ ሲገኝ፣

⑩) ከ1.5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ንጹሐን ከመኖሪያ ቤታቸው ተፈናቅለው በመጠለያ ካምፖች፣ በት/ቤቶች፣ በሆስፒታል ግቢዎች፣ በመስጂዶችና ቤተ ክርስቲያን ተጠልለው ሳለ በዛው ባሉበት ጥቃቱ ሲያገኛቸው…

(ከሰው ነፍስ አይበልጥምና ወደ አመድነት ስለተቀየሩት ውብ ህንፃዎችና መሠረተ ልማቶችማ አውርተን አንዘልቀውም።)

የሰለጠነ ተብዬው ዓለም አሁንም «ጦርነቱ ይቁም!» ከማለት ይልቅ «እስራኤል ራሷን የመከላከል መብት አላት፣ ሐማስ መጥፋቱን ማረጋገጥ አለባት፣ ከጎንሽ ነን፣ ሐማስ ሽብርተኛ ነው፣ በሐማስ ጥቃት ለሞቱተረ እስራኤላዊያን አዝነናል!…» እያሉ ነው።

ትንሽ አሻሻልን የሚሉት ደግሞ ጦርነቱ መቆም የለበትም፤ ግን የተወሰነች እርዳታ ይግባላቸው ይላሉ።

እስካሁን በጋዛ መብራት የለ፣ ውሃ የለ፣ ምግብ የለ፣ ነዳጅ የለ…። በዚህ የተነሳ የቆሰሉትና መደበኛ ህመም የሚታመሙትም መታከም አልቻሉም።

ዙሪያውን በከበባ ስለሆነ ለጠናበት ታማሚ የውጭ ሕክምና እንዲያገኝ ማድረግ አልተቻለም።

እስራኤል ከላይ በአየር ከምታዘንበው የቦምብ ዝናብ ባሻገር ከምግብና ውሃ እንዲሁም ከሕክምና ከልክላ በጅምላ ጭፍጨፋ የጦር ወንጀልና የዘር ማፅዳት ወንጀል በመፈጸም ላይ ትገኛለች። ይህ ሁሉ የሚሆነው ዓለም እያዬ በ21ኛው ክፍለ ዘመን ነው። ተመድ ተብዬውም ሆነ የትኛውም የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ነኝ የሚል ተቋም ሁሉ የውሃ ሽታ ሆኗል። የነርሱ ህግ እነርሱን ለማዳን እንጂ ለሌላው አይሠራም። እነርሱ ዘንድ የሙስሊም፣ የዓረብና የአፍሪካዊ ሞት ከውሻቸው ሞት በታች ነው።

ግን ነፍስ ሁሉ እኩል ናትና የእጃቸውን አንድ ቀን ማግኘት አይችሉም። ነገ ላይ በሌላ የነርሱ አካል ላይ ጥቃት ሲፈጸም በሚዲያቸውም ሆነ ባልተጻፈው ህጋቸው ከአጥናፍ እስከ አጥናፍ ሲለፍፉ እናገኛቸዋለን።

አላህ ውርደታቸውን ያቅርበው፤ ለተበዳዮች ነስሩን ያፍጥነው።

አላህ የአሸናፊዎች ሁሉ አሸናፊ የሆነ ጥበበኛና ታጋሽ ጌታ ነው። አንድ ቀን አይርላቸውም።

||

t.me/MuradTadesse

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group