UMMA TOKEN INVESTOR

Obsineeti123 Сhanged his profile picture
6 month
Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Obsineeti123 shared a
Translation is not possible.

እጅግ ልብ የሚነካ ታሪክ

▰▰▰✿▰▰▰

አንድ ሰአለባህ ኢብን፣አቢ- አብድረህማን የሚባል የ16 ዓመት

ልጅ ነበር። ይህ ታዳጊ ወደ አኪራ በሄደ ጊዜ የእሱን ጀናዛ

ለማጀብ መላኢካዎች ወርደዋል፣ክስተቱ እጅግ ልብ

ይነካል፣በትእግስት ያንብቡት ታሪኩ እንዲህ ነው....

አንድ ቀን ረሱል ( ሰ.0.ወ) ይህ ሰአለባህ ኢብን፣አቢ-

አብድረህማን የተባለውን የ 16 አመት ልጅ፣ወደ አንድ ቦታ

ይልኩታል።በጉዞ ላይ ሳለ መንገድ ላይ በድንገት አንዲት ሴት በሯን

ከፍታ ገላዋን ስትታጠብ ይመለከታታል።አይኑ ባሳየው ነገር

ተፀፀተ

:

ይህ ልጅ አስቦበት ሳይሆን ንፋሱ መጋረጃውን ሲከፍተው በድንገት

ነበር ያያት።እናም ይህ ልጅ በጣም ደነገጠ። እንዲህም አለ ረሱል

(ሰ.0.ወ) ልከውኝ እንዴት እንደዚህ አይነት ነገር እመለከታለው?

በማለት እራሱን ወቀሰ።

ታድያ ይህን ሀራም ነገር አይቼ እንዴት ብዬ ነው ረሱልን

(ሰ.0.ወ ) የማየው ? አይሄንም ሀራም ባየሁበት አይኔማ ረሱልን

አላይም ብሎ የተላከውን ሳይመልስ በዛወ ይጠፋል።ሳይመለስ

ቀረ፣ ረሱል ( ሰ.0.ወ ) የዚህ ልጅ መጥፋት አሳሰባቸውና ሁለት

ሰሀቦችን እንዲፈልጉት ይልካሉ።

ሰሀቦቹም መዲና ድረስ ሄደው ፈልገው ሊያገኙት አልቻሉም

ለረሱል

( ሰ.0.ወ ) ልጁን እንዳጡት ይነግሯቸዋል።

ረሱል ( ሰ.0.ወ ) ጉዳዩ እጅጉን ስላሳበቸው ለሁለተኛ ጊዜ

ሌሎች ሰሀቦችን አክለው አሁንም፣ ደግመው ልጁን እንዲፈልጉት

ይልኳቸዋል። ሰሀቦችም እሱን ፍለጋ ዞረው፣ ዞረው መጨረሻ ላይ

አንድ ገበሬ ዘንድ ይደርሳሉ። ገበሬው ገና ሲያያቸው እርዳታ ፈላጊ

መሆናቸውን ሲያውቅ ምን ልርዳቹ በማለት ጠይቆ

ያስተናግዳቸዋል።

እነሱም እንዲህ አይነት ልጅ አይተሀል? ብለው በዙ

የሚያውቁበትን ምልክት ይነግሩታል። ምልክቱን ሲነግሩት፣

ሰወየው ልጁን ወዲያው አወቀው፣

:

ከዚያም ይህ ልጅ እኮ እዛጋ የምታዩት ተራራ ላይ ነው የሚኖረው፣

ምን እንደነካው እንጃ ሁል ጊዜ ያለቅሳል ፣እያለቀሰ

( አስተግፊሩሏህ ) እያለ ጌታውን ምህረት ይጠይቃል፣

( አስተግፊሩሏህ) ሲል ነው የሚውለው፣ ልጁ ከማንም

አይገናኝም መሸት ሲል ማታ አካባቢ እኛ ጋር እየመጣ፣ ወተት

ይጠይቀናል

:

ከዚያም ወተቷን ፊት፣ለፊቱ ያስቀምጣትና እንባውን ወተቷ ላይ

እያፈሰሰ ያቺን ፣ወተት ጠጥቶ ይሄዳል ። በተረፈ ከማንምጋ

አይገናኝም በማለት የልጁን ሁኔታ በሀዘን ነገራቸው።

:

ሰሀቦች ተገረሙ የተባሉትንም በመስማት የሚመጣበትን ሰዓት

እንጠብቅና ሲመጣ ረሱል ( ሰ.0.ወ ) ዘንድ ይዘነው እንሄዳለን

ተባባሉ ፣እናም ቀኑ መሸ እና ልጁ በተባለበት ሰዓት ላይ ወተት

ሊጠይቅ ሲመጣ ሰሀቦቹ ያገኙታል ፣ልጁ ሲበዛ ከስቷል፣ በሀዘን

ምክንያት ተጎሳቁሏል በጣም አዘኑ

:

ልጁንም ያዙትና ወደ ረሱል (ሰ.0.ወ ) ዘንድ ሊወስዱት

እንደሚፈልጉ ሲነግሩት ፍቃደኛ አልሆነም፣ መሄድ እንደማይችል

በጣም አጥብቆ ነገራቸው፣ በደከመ ጉልበቱ ከእጃቸው

ሊያመልጥም ፈለገ ። ነገር ግን ጉልበት እንደሌለው ስላወቁ

በግድ፣ ተሸክመው ወደ ረሱል ( ሰ.0.ወ ) ዘንድ ወሰዱት።

እርሳቸው ዘንድም ደረሱ ፣ረሱልም ( ሰ.0.ወ ) ና- እስቲ ብለው

ጭንቅላቱን ታፋቸው ላይ ሊያስተኙት ሲሉ፣ ጭንቅላቱን ከታፋቸው

ላይ በማንሳት ( ያረሱለላህ ) ይህ የኔ ጭንቅላት በጣም ብዙ

ወንጀል ተሸክሟል ስለዚህ የርስዎ የተከበረ አካል ላይ አታስተኙኝ

በሎ ገሰጻቸው

:

ልጁ ረሱል (ሰ.0.ወ)-ጋ በደረሰ ጊዜ ከመክሳቱ የተነሳ በጣም

ጎስቁሎ የሞት ጥላ በእሱ ላይ አጥልቶ ጣረ ሞት ላይ ነበር።እናም

አይኑ ድንገት ባየው ነገር ተፀፅቶ በተራራ ጫፍ ላይ ቁጭ ብሎ

እያለቀሰ (አስተገፊሩላህ) እያለ የጌታውን ምህረት እየጠቀ ቆይቶ

በመጨረሻም

ሸሀዳ ይዞ በረሱል ( ሰ.0.ወ ) እጅ ላይ ሞተ (ወደ አኪራ ሄደ) ።

ከዚያም ጀናዛው ታጥቦ ወደ ቀብር መሄድ ጀመረ፣ ጀናዛውን

ተሸክመው በሚሄዱበት ሰዓት የረሱል ( ሰ.0.ወ ) አረማመድ

ይለይ ነበር። ረሱል (ሰ.0.ወ) በእግር ጣቶቻቸው ይራመዳሉ።

ሰሀቦችም ረሱል (ሰ.ዓ.ወ) መንገድ የተጣበበባቸው መስሏቸው

ሰዎችን እየገፈታተሩ፣ መንገድ ይከፍቱላቸዋል።ነገር ግን አሁንም

ረሱል (ሰ.0.ወ) እንደመጀመሪያው ነበር በጣታቸው የሚጓዙት

ሰሀቦች በርሳቸው አረማመድ ግራ፣ተጋቡ ፣ተገረሙ እንዲህም ሲሉ

ጠየቋቸው ?

ያ-ረሱለላህ ( አንቱ የአላህ መልእክተኛ ሆይ )ምነው መንገዱ

ክፍት ሆኖ ሳለ ለምን በእግር ጣቶቾዎ ይራመዳሉ አሏቸው

ረሱልም እንዲህ በማለት መለሱላቸዋል።

የ(ሰዕለባህ ኢብን፣ አቢ-አብድረህማን)-ን ጀናዛ ለማጀብ የመጡ

መላኢካዎች ፣ብታዩዋቸው ኖሮ፣ከብዛታቸው የተነሳ አንድ እግር

እንኳን ለማስቀመጥ የሚመች ቦታ አታገኙም ነበር ብለው

ነገሯቸው።

የዚህን ታዳጊ ምርጥ የአላህ ባርያ ታሪክ ወደውታል ?

ታሪኩ ለአሁኑ ትውልድ፣ ይሆናል ያስተምራል ብለው ካመኑ፣

እርሶዎጋ ብቻ እንዳይቀር ሼር በማድረግ ለወዳጅ ዘመዶዎ ያካፍሉ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group