UMMA TOKEN INVESTOR

Tentang saya

ቀጥተኛውን መንገድ አሏህ ይመራኝ ዘንድ የዘውትር ዱዓዬ እና ምኞቴ፣ተስፋዬም ነው።

Tidak bisa diterjemahkan.

ሳዑዲን ያስጨፈረው ዲጄ፣

በጋዜጠኛ የኑስ ሙሃመድ የተፃፈ:-

በሳዕዲ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የታየው በዲጄዎች የታጀበ የጭፈራ ምሽት የዓለም ሙስሊሞችን አሳዝኗል። የአሳዛኝነቱ ምክንያት ምን እንደሆነ ለሁላችንም ግልጽ ሲሆን ብዙ ሰው የማያውቀውና ሙስሊሙን ጽኑ ድንጋጤ ውስጥ የከተተው ግን ነብዩ ሙሐመድ ሱዐወ ስለዚህ ዘመንና ስለአገራቸው የተናገሩትና ተፅፎ የተቀመጠው ነገር በዚህ በኛ ዘመን በመድረሱ ነው። ብዙዎች እንዳትረክስ ሲሳሱላት የነበረችው የነብዩ ሀገር በአሁኑ ንጉሷ የተነሳ ሌላ ማጥ ውስጥ እየገባች ነው ሲሉ የሚናገሩ ብዙ ናቸው።

እኔን የገረመኝና ይህን ጽሑፍ እንዳጋራችሁ ያደረገኝ ግን የሙዚቃ ኮንሰርቱ መከናወን ብቻ ሳይሆን ዲጄው ከጭፈራው በኋላ ለሚዲያ የሰጠው እጅግ በጣም አስገራሚና ለአንድ አማኝም አሳዛኝ የሆነ ቃለመጠይቅ ነው።

ጋዜጠኛዋ እንዴት ነበር ኮንሰርቱ? በሳዑዲ ታሪክ የመጀመሪያ እንደመሆኑ ምን ፈጠረብህ? የመፈቀዱ ምስጢርስ ምንን ያሳያል? አለችው፦

ዲጄው በከፍተኛ ደስታና መደነቅ ውስጥ ሆኖ መመለስ ጀመረ፦

"ይህ እጅግ በጣም ያስደነቀኝ ታሪክ ነው... በሳዑዲ አረቢያ ሴትና ወንድ አብረው ሲጨፍሩ ማዬት አስባችሁታል... እንዴት ደስ ይላል!? ገና ደሞ ወደፊት ብዙ ብዙ ነገር ይፈቅዳል ብለን እንጠብቃለን... ይህ መበረታታት ያለበት ጥሩ ጅምር ነው..."

ዲጄ ዴቪድ ጉታ "ገና ወደፊት ብዙ ነገር ይፈቀዳል.." ያለው ምን እንደሆነ መንገር አንባቢን ማድከም ነው። የሆነ ሆኖ ምዕራባውያን ትንሽ ቀዳዳ ሲያገኙ ከሰይጣን የባሰ መጥፎ ድርጊታቸውን ወደ አንዲት ሀገር እንዴት እንደሚያስገቡት የዚህን ሰው ንግግርና የፊት ሁኔታ አይቶ ብቻ መረዳት ይቻላል።

ዲጄው በዓለም ደረጃ ታዋቂ ነው ሌላ የትም ሀገር ዞሮ ያስጨፈረውና ራቂት ያስደነሰው ለሱ በቂ አይደለም ሳዑዲም ወደዚህ የአደባባይ መጠጥና ባህለ ወጥ ጭፈራ መቀላቀል አለባት ማለት ነው!? በአጋጣሚ በሸሪአ የምትተዳደር የሙስሊም ሀገር ሆና እንዲህ አሉ እንጂ የክርሥትያን ሀገርም ሆና በሳዑዲ ልክ ጥብቅ ህግ ቢኖራት ዲጄዎቹ ይሄን ከማድረግ ወደ ኋላ አይሉም ነበር።

ዓለማችን ለሙስሊምም ለክርሥትያኑም ከወትሮው በተለዬ ሁኔታ እየከፋች ነው። የአንዱ መኖር ለአንዱ አስፈላጊ የመሆኑን ያህል ያንዱ መርከስም ለሌላው መርከስ ነው። ሰሞነኛውን ነገር ሁሉ ላስተዋለና መንፈሳዊ እውቀት ላለው ሰው በምድራችን ላይ ምን እየመጣ እንደሆነ... ከዛስ ምን እንደሚከተል ለመተንበይ ግልጽ ነው።

ይህ በሰው ልጆች ታሪክ ውስጥ ቀደምት እንደታዩት እና በአደባባይ ወንጀላቸው የተነሳ ከምድረገጽ እንዲጠፉ የተበየነባቸው ህዝቦች ዓይነት 'ግልጽ ሀጢያት' የሚሰራበት ዘመን ነው።

ነገ ከሞት በኋላ ከፈጣሪ ፊት ቀርበን እንጠየቃለን ብለን ለምናምን የሰው ልጆች ሁሉ ፈጣሪ መልካም እሴቶቻችንን፣ ባህላችንንና እምነታችንን ይጠብቅልን።

👇

Kirim sebagai pesan
Bagikan di halaman saya
Bagikan di grup
Tidak bisa diterjemahkan.

አለማችን በዲሞክራሲ ስም ተለውሳ ውድቀትና ኪሳራ ላይ ነች። ምዕራባውያን እና አውሮፓውያን ዲሞክራሲን አብዝተው እንደመስበካቸው ሳይሆኑ በፀረ ዲሞክራሲ እና ፀረ ሰበዓዊነት ጨቅይተው፣እነሱን ያልመሰለን ማለትም በእምነቱ ወይም በአመለካከቱ ያልተመሳሰላቸውን ለማጥፋት ቆርጠው የተነሱ ፀረ ሰውነት ባህሪያትን የተላበሶ አውሬዎች የበዙባት አለም ሆናለች!

Kirim sebagai pesan
Bagikan di halaman saya
Bagikan di grup
Tidak bisa diterjemahkan.

"አንድ ሰው በጋዛ ስለተፈጠረው ነገር ዝም ካለ ልብ የለውም።" ፑቲን

Kirim sebagai pesan
Bagikan di halaman saya
Bagikan di grup
Tidak bisa diterjemahkan.

ያ ረቢ! ፍልስጤሞችን አንተው ታደግልን!

image
Kirim sebagai pesan
Bagikan di halaman saya
Bagikan di grup
AbuLizaDawud berbagi sebuah
Tidak bisa diterjemahkan.

" ሀማስ የማይችለውን ጦርነት ከፍቶ ፍልስጤሞችን አስጨረሳቸው "

ይህ የፈሪዎቹ ወቀሳ ነው ! ይህ የደንታቢሶቹ ክስ ነው ! ይህ የኢስላም ልቅናም የሙስሊሞች ክብርና ህልውናም የማያሳስባቸው የግደለሾች ክስ ነው !!

ሀማስ የተመሰረተው በ 1987 ነው ከዛሬ 36 አመት በፊት ። እስራኤል ፍልስጤማዊያንን ካለአንዳች መከላከል እንደፈለገች ስትጨፈጭፍ ህይወታቸውን ሰውተው ህዝባቸውን ለማዳን የኢስላም ሸአኢሮችን ለመጠበቅ ሞትን ላይፈሩ ተማምለው የመሰረቱት የሙጃሂዶች ስብስብ ነው ። ይህ የነ ሸይኽ አህመድ ያሲን የነ አብዱአዚዝ አልረንቲሲ የህይወት መስዋእትነት ውጤት ነው ።

ሀማስ ባይኖር በአሁኑ ሰአት አንድም ፍልስጤማዊ በፍልስጤም ምድር አይገኝም ነበር ። ጋዛ ዌስት ባንክ የሚባሉ የፍልስጤም መኖሪያዎችንም አናይም ነበር ። የእስራኤልን እጅግ አረመኔያዊ ጭፍጨፋ የሚታገል ብቸኛው የሙጃሂድ ቡድን ሀማስ ብቻ እንጅ ሌላ አይደሉም ።

ሀማሶች ከላይ ሚሳኤሉ ቢዘንብባቸው ከታች ታንክና መድፉ ቢያጓራባቸው እንኳን የሚፈራ የሚደነግጥ ልብ የሌላቸው ተዋርዶ ከመኖር በክብር ሸሂድ መሆንን የሚናፍቁ ሙጃሂዶች ፤ መላው አረብ ተንቦቅቡቆ ከእስራኤልና ምእራባውያን ጋር ሲሽለጠለጥ እነርሱ ግን ከተራራ በገዘፈ ኢማናቸው ተመክተው እነዚህን የገጠሙ የሶሀቦች ትውስታ ትክክለኛ ኸሊፋዎቻቼው ናቸው ። ሀማሶች አንድም ቀን ተመችቷቸው ኖረው አያውቁም ። ሁሌም ከምድር በታች እየቆፈሩ ከምድር በታች እየኖሩ አፈር ለብሰው ድንጋይ ተንተርሰው ይሄንን የሞተ ኡማ ሩህ አለው የሚያስብሉ የኡማውን ቀንደኛ ጠላት እስራኤልን እያቃዡ የሚያስጨንቁ እነርሱ የሙሀጅርና አንሷሮች ኩትኩት የውዱ ነብያቸውም ፈለግ እውነተኛ ተከታይ ፤ ኢስላምን በቃል ሸንገላ ሳይሆን በተግባር የሚኖሩት ፤ ጅሀድን በቂርአት ሳይሆን በህይወትና ንብረታቸው የሚማሩት የወቃሽን ወቀሳ ሳይሰሙ ስለኢስላማቸው ስለህዝባቸው ፍግም የሚሉ እነርሱ ህያዋን ናቸው ።

የፈሪ ፈሪዎቹ ግን አህያውን ፈርቶ ዳውላውን እንዲሉ እስራኤልን ሲፈሩ ሀማስን ይወቅሳሉ ! ሀማስን ያወግዛሉ !  ይህ ንፍቅና ነው ! ይሄን በቃል መግለፅ አልችልም !!

እነዚህ ደንታቢሶች ሀማስን " ካለአቅሙ እስራኤልን እየተዋጋ " ብለው ጀግኖቹን ለማውገዝ ሲሞክሩ አይሰቀጥጣቸውምን ? በአቅምማ ቢሆን የሳኡዳ አረቢያ የኢኮኖሚ አቅም የእስራኤልን ሁለት ሶስት እጥፍ ይበልጥ ነበረ ! የግብፅ ወታደር ብዛት የእስራኤልን ሶስት እጥፍ ይበልጥ ነበረ ! የቱርክና የፓኪስታን ወታደራዊ አቅም ከእስራኤል ይልቅ ነበረ !

ግና ከነርሱ ጋር የኢኮኖሚና ወታደራዊ አቅም እንጅ የሀማሶች ሪጃልነት የለም !! ሪጃልነትን አላህ መርጦ የሰጠው ለሀማሶች ናቸውና ! የእርሱን ጅሀድ ይዋደቁ ዘንዳ የተመረጡት ሀማሶች ናቸውና !!

ሌላውማ መይት ነው ! ኢራንና ሂዝቦላህ ለሙስሊሞች ክብር ያላቸውን መቆጨት ለምእራባዊያን ያላቸውን ትግል 1% እንኳ የላቸውም !!

አህሉል ሩዞችና አህላል ፊራሾች አህለል ጅሀዶችን ሲያንጓጥጡ እንደማየት የሚያሳፍር የለም !

ሀማስ ይህንን ጦርነት የጀመረው እስራኤል መስጅደል አቅሷን ጨርሳ ጠቅልላ ለመውሰድ እየተዘጋጀች ባለችበት ነበር ። እናም የአይሁድ አማኞች መስጅዱን ሊረከቡ ዝግጅታቸውን እየጨረሱ ሳሉ ነበር ሀማስ እኛ በህይወት እያለን ይህንን አንፈቅድም በማለት ጦርነት ያወጀው ።

ሀማስ ጦርነቱን ሲከፍት እስራኤል በወረራ በያዘቻቼው የጋዛ ድንበሮች ላይ ምእራባውያን ሙጅሪሞችን ጨምሮ የእስራኤል ሰፋሪዎች በጋዛ ድንበር ተሰባስበው እየጠጡ እየጨፈሩ ነበር ። ሀማስ እንደ መብረቅ ወረደባቸው ። በመቶዎች የሚቆጠሩ የእስራኤል ወታደሮችንም ወደ ጀሀነም ላካቸው ። ከዚያ በሗላ ይሄው ጦርነቱ ተፋፍሞ ቀጥሏል ።

እስራኤል አቅሟ ንፁሀን ላይ ነውና ንፁሀንን በአየር እየጨረሰች ነው ። ይህንን ከምስረታዋ ጀምሮ የምታደርገው ነው ። ሀማስ ስለመጣ እስራኤል ጦርነት የከፈተች የሚመስላቸውን ገልቱዎች ማስረዳት ከባድ ነው ።

አላህ ድልን ለሙጃሂዶቹ ያጎናፅፋል !

ቃሉንም ይሞላል !

ያኔ መናፍቃንም አዱወሎሆችም ያፍራሉ ይሸማቀቃሉ ኢንሻአላህ !!!!

#seid_mohammed_alhabeshiy

image
Kirim sebagai pesan
Bagikan di halaman saya
Bagikan di grup