UMMA TOKEN INVESTOR

abu fadil قام بمشاركة
لا يمكن الترجمة

በጨለማ ተጓዦችን… አበስራቸው‼

========================

✍ ምናልባትም ቀን ላይ ላብ ጠብ በሚያደርግ የጉልበት ሥራ ላይ አሳልፈህ ይሆናል፣ ናላን በሚያዞር የጭንቅላት ሥራ ተወጥረህ ይሆናል፣ በጠዋት የወጣህ ወደ ቤትህ የምትገባው አምሽተህ ይሆናል፣ ርቦህ ደክሞህ መጥተህ ትንሽ አረፍ እንዳልክ የፈጅር ሶላት ይደርስና በዙሪያህ ባሉ መስጂዶች «ሶላት ከእንቅልፍ በላጭ ነው፣ ኑ ወደ ሶላት፣ ኑ ፈላሕ ወደምትወጡበት መንገድ…» የሚል የጌታህን ጥሪ በአላህ ባሮች አንደበት ትሰማለህ።

ያኔ ነፍስህ በእንቅልፍ ሰመመን ውስጥ ሆና ከላይህ ላይ ያለውን ብርድልብስ አሽቀንጥረህ፣ ያንን ጣፋጭ እንቅልፍ ትተህ ለጌታህ ትዕዛዝ ምላሽ ለመስጠት ትነሳለህ ወይንስ «ቆይ ትንሽ እንቅልፌ ይውጣልኝና እነሳለሁ!» በሚል ሽንገላ ባልሰማ ጸጥ ብለህ ጸሐይ ሲወጣ መስገድ?  መቼም ከናካቴው አለመስገድ ይኖራል ብዬ አላስብም። አላህ ይጠብቀንና!

ፈጅር ላይ ከዚያ ደክሞህ ካገኘኸው ጣፋጭ እንቅልፍ ለመነሳት እነዚህ 3 ሐዲሦች በቂ ናቸውና ላስታውስህ ወደድኩ።

①ኛ) ለአንተ ገና ሳያዩህ በትካዜ የናፈቁህና  ሁሌም የሚቆረቆሩልህ አዛኙ ነቢይ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦

(بشرِّ المشائينَ في الظلمِ إلى المساجدِ، بالنورِ التامِّ يومَ القيامةِ)

«በጨለማ ወደ መስጂድ ተጓዦችን የውመ-ል-ቂያማህ በሙሉ ኑር (ብርሃን) አበስራቸው።»

[ጃሚዑ-ስ'ሶጚር: 2129፣ ሶሒሕ አቡ ዳውድ: 561]

√ ያኔ የውመል ቂያማህ ሁሉም ሰው በጭንቅ ውስጥ ሆኖ፣ ታላላቅ ነቢያትና የአላህ መልዕክተኞች ﷺ ሳይቀሩ «ነፍሴ ነፍሴ» በሚሉበት ቀን፣ ከፊሉ ሰው በጸሐይዋ ንዳድ ላቡ እስከ አፍንጫው ድረስ ሲያሰምጠው፣ ወደየት ልሽሽ፥ ወደየት ልግባ በሚልበት የጭንቅ ቀን… «ሙሉ በሆነ ኑር» ከመበሰር የበለጠ ምን መታደል አለና ነው ፈጅር ሶላት ላይ የምትዘናጋው?

ይሄን ብስራት የነገረህ እኮ ተራ ሰው ሳይሆን የሁሉም ፈጣሪና ባለቤት የሆነው አላህ የላካቸው ውድ ነቢይ ﷺ ናቸው። በል ተነስ!

*

②) ነቢይህ ﷺ እንዲህም ብለዋል፦

(مَن صَلَّى الصُّبحَ فَهُوَ فِي ذِمَّةِ اللَّهِ…)

«ሱብሒን (የፈጅር ሶላትን) የሰገደ ሰው በአላህ ጥበቃ ስር ነው።»

[ሙስሊም: 657]

√ እና እንደ ሙስሊም በአላህ ጥበቃ ስር ከመዋል የበለጠ ምን መታደል አለና ነው የምንዘናጋው? አላህ በጥላው ስር ካዋለህ አንተን የሚዳፈር ሁሉ ጥላውን እንደተዳፈረ ነውና የሚከላከልልህ አላህ ነው። ምክንያቱም ራስህን ለርሱ ሰጥተሃልና! ያ ሊጎዳህ ያለ ሁሉ ከአላህ በታች የሆነ አንድ ተራ ፍጡር ነውና በጥበቡ አደብ ያሲዘዋል።

√ አዕመሽ እንዳስተላለፈው በአንድ ወቅት ሳሊም (የዐብደ-ል'ሏህ ኢብኑ ዑመር ልጅ) ከሐጃጅ አጠገብ ቆሞ ነበርና (ያው ሐጃጅ ኢብኑ ዩሱፍ እንደምታውቁት…) አንዱ በአጠገቡ ሲያልፍ አየና ሐጃጅ ለሳሊም "የዚህን ሰው አንገት በሰይፍ ቅላው!" ብሎ አዘዘው። ሳሊምም የታዘዘውን ለመፈጸም ሰይፉን እንዳነሳ… ለሰውየው «ፈጅርን ሰግደሃል?» አለው። አንገቱ ሊቀ'ላ የነበረው ሰውየም «አዎ» ሲል መለሰ። ሳሊምም «በል! እንዳሻህ ጉዞህን ቀጥል!» አለውና ወደ ሐጃጅ ተመልሶ ይዞት የነበረውን ሰይፍ ጣለው። ሐጃጅም ለሳሊም «አንገቱን ቀላኸው?» ብሎ ጠየቀው። ሳሊምም «በጭራሽ» አለው። ሐጃጅም «ለምን?» አለው። ሳሊምም «እኔ አባቴ (ዐብደ-ል'ሏህን ማለቱ ነው) ነቢዩ ﷺ "የጠዋትን (የፈጅርን ሶላት) የሰገደ ሰው እስከ ምሽት ድረስ በአላህ ጥበቃ ስር ነው!" ብለዋል ሲል ሰምቸዋለሁ።» ብሎ መለሰለት። «በአላህ ጥበቃ ስር ያለን ሰው አልዳፈርም!» ማለቱ ነው።

√ ታላቁ የዘመናችን ዐሊም ኢብኑ ዑሠይሚንም ይሄን ሐዲሥ አስመልክተው በሪያዽ ሸርሓቸው ላይ ትንታኔያቸውን ሲያሰፍሩ እንዲህ ብለዋል፦

" في هذا دليل على أنه يجب احترام المسلمين الذي صدَّقوا إسلامهم بصلاة الفجر ؛ لأن صلاة الفجر لا يصليها إلا مؤمن ، وأنه لا يجوز لأحد أن يعتدي عليهم)

«ይህ እነዚያን በፈጅር ሶላት እስልምናቸውን ያረጋገጡ ሙስሊሞችን ማክበር እንደሚገባ ማሳያ ነው። ምክንያቱም የፈጅር ሶላትን ሙእሚን እንጂ አይሰግዳትም። ስለሆነም ማንኛውም ሰው ድንበር ሊያልፍባቸው አይገባም።»

[ሸርሕ ሪያዹ-ስ'ሷሊሒን: 1/591]

ምንም እንኳ እስልምናችን በማንም ንጹሐን ላይ ድንበር ማለፍን ቢከለክልም፤ ጭራሽ በእንዲህ አይነት ባሮቹ ላይ ድንበር ማለፍን ደግሞ የክልከላ ጥግን ከልክሏል።

*

③ኛ) ሐቢቢ! የፈጅርን ሶላት ፈርዱን መስጂድ ሂዶ መስገድ፤ አይደለም ፈርዱን መስገድ ሱን'ናውን መስገድ ብቻውን ያለውን ደረጃ አልሰማህም? ወይንስ ሰምተህ መተግበር ተሳነህ?

ውዱ ነቢያችን ﷺ ምን እንዳሉ ልንገርህ፦

ሐዲሡን ያስተላለፈችው ራሷ ባለቤታቸው እናታችን ዓኢሻህ (እውተኛዋ የእውነተኛ ልጅ) ናት - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና። ውዱ ነቢይ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦

(ركعتَا الفجرِ خيرٌ من الدُّنيا وما فيها))،

«የፈጅር 2 ረከዓዎች (ሱንናዎቹ)፤ ከዱንያና በውስጧ ካለው ይበልጣሉ።»

[ሙስሊም: 725]

وقال أيضًا እንዲህም ብለዋል ﷺ፦

 ((لهُما أحبُّ إليَّ من الدُّنيا جميعًا)

«እነርሱ ለኔ ከዱንያ ሁሉ የተወደዱ ናቸው።»

አስበው! ዱንያ ላይ ስንት ገንዘብና ስንት ስልጣን አለ?

በየሃገራቱ ያሉ ውብና ሃብታም መንደሮችን፣ ዘመናዊ መኪኖችንና መኖሪያ ቤቶችን፣ የቅንጦት መዝናኛዎችን… ስንቱን ልዘርዝርልህ። ስታየው የሚያስቀና ስንትና ስንት ነገር አለ። «እኛም ከነዚህ ጋር እኩል እዚህች ዓለም ላይ እየኖርን ነው?» የሚያስብሉ ስንትና ስንት ቅንጡ ኑሮዎች አሉ?

ግን ምን ዋጋ አለው? የፈጅርን እንኳን ፈርዱን ሱ-ን'ናውን መስገድህ ብቻ ከዚህ ሁሉ ይበልጣል። የሱን'ናው ትሩፋት እንዲህ ከሆነ ፈርዱ ምን ቢሆን ነው በአላህ!

ኧረ! ያ አኺ! ተነስ እንነሳና ፈጅርን እንስገድ! ደግሞ ለዚህች ለማትሞላና ብትሞላ እንኳ ነገ ጥለናት ለምንሄዳት ዱንያ ብለን ይሄን ሁሉ ትሩፋት እናስመልጥ እንደ?  ትንሽ ደቂቃ እኮ ናት ሐቢቢ! 24 ደቂቃ እንኳ ላትሞላ ትችላለች! ታዲያ እንደት ከ24 ሰዓቱ ውስጥ 24 ደቂቃ ለጌታህ ትዕዛዝ ምላሽ ለመስጠት አጣህ? የተፈጠርከው እርሱን ለመገዛት ሆኖ ሳለ ሙሉ ጊዜህን መስጠት ባትችል እንኳ 24 ደቂቃ መስጠት ተሳነህ? አስበው!

24 ደቂቃ በስንት እንደምታልፍ! ከጓደኛህ ጋ ሻይ ቡና እንበል ብለህ ስንት ሰዓታት ነው የምታሳልፈው? ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ስንት ሰዓት ነው የምታሳልፈው? ኳስ… ገለመሌ እያልክ ምን ያክል ሰዓት ነው የምታሳልፈው? ታዲያ የባለዚሁ ሰው እንደት ይህቺን ታክል ደቂቃ ለሶላት መስጠት ከበደህ? ኧረ! ተው ሐቢቢ ተው! ብልጥ ሁን!

የላ! ፈጅር አዛን ሲል ወደ መስጂድ! የምን እየሰሙ መሟዘዝ! የምን አላርም አለመቅጠር ወይም የቀጠሩትን ማጥፋት!

አላህ ያግራልን! ውዶች አንዘናጋ! የፈጅርና የዒሻእ ሶላት ለሙናፊቆች ለማስመሰል እንኳ የማይመቹ የአማኝነት ማረጋገጫ ናቸውና እንበርታ። 

*

ለሌሎችም የፈጅር መስገድ መነሳሳት ሰበብ ከሆንን (ለአንድም ሰው ቢሆን) መልዕክቱን እናድርሳቸው።

||

ወንድማችሁ፦ ሙራድ ታደሰ

=========

أرسل كرسالة
شارك على صفحتي
شارك في المجموعة
abu fadil قام بمشاركة
لا يمكن الترجمة

የጎዳና ላይ ዳዕዋ‼

==============

✍ ከአሁን በፊት አልፎ አልፎ ቢሆንም በአንዳንድ በጎ ፈቃደኛ ወንድሞች የጎዳና ላይ ዳዕዋ እያደረጉ ነበር። ከዚህ በፊት በተበታተነ መልኩ ሙከራ ሲደረግበት የነበረው የጎዳና ላይ ኢስላማዊ ዳዕዋ ከሚመለከተው አካል ሙሉ የዕውቅና ፈቃድ አግኝቶ በተጀራጀ መዋቅር ሥራ መጀመሩ ተበስሯልና ሁላችሁም እንኳን ደስ አላችሁ።

በአላህ ፈቃድ መንገዶች ሁሉ ወደ ኢስላም ያመራሉ። የ"ላ ኢላሃ ኢለ'ልህ" ጥሪ የሁሉንም በር ያንኳኳል።

ሁላችንም በሞራልና መሰል በሚያስፈልጓቸው ድጋፎች ሁሉ ከጎናቸው በመቆም ልናበረታታቸው ይገባል።

ቪድዮ፦ ዛሬ ቤተል አካባቢ የተደረገ የጎዳና ላይ ዳዕዋ

||

t.me/MuradTadesse

7 وجهات النظر
أرسل كرسالة
شارك على صفحتي
شارك في المجموعة
لا يمكن الترجمة

ከረሱል ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም የተላለፉ 10 ትልላቅ የቂያማ ቀን ምልክቶች:-

1 የደጃል መምጣት !

2 የመርየም ልጅ ነብዩሏህ ኢሳ (ዐሰ) ደጃልን ለማጥፋት ከሰማይ መውረድ!!

3. የየዕጁጅ እና መዕጁጅ መምጣት !

4. በስተ ምስራቅ የ 1ከተማ መሬት መደርመስ ክስተት ማለትም ከተማዋ የት እንደገባች እስማይታወቅ ትጠፋለች። (ትሰምጣለች)

5 ደግሞ እንደዚሁ በስተ ምዕራብ አንድ ትልቅ ከተማ ተገለባብጣ ትጠፋለች።

6 ብዙ የአረብ ግዛት መሬት ይደረመሳል ሰዎች ምድር ምን ነካት?? እያሉ ይነጋገራሉ !

7 ብርቱ የሆነ ጭስ ይነሳል በሰማይ ና በምድር ይሞላዋል ለአማኞች ወረርሽኝ ሲሆን ለከሃዲዎች ቅጣት የሆነ።

8 ፀሀይ በመግቢያዋ ትወጣለች ያኔ መላኢካዎች ብዕራቸውን ያስቀምጣሉ። የተውበት በር ይዘጋል። የመልካም ስራ የመጥፎ ስራ የሁሉ ነገር መቀበያ መዝገብ ይዘጋል።

9 አንድት እንሰሳ ትወጣለች ሰዎችን ምታናግር የሆነች ከሃ* ዲውን ከሃ* ዲ ሙዕሚኑን ሙዕሚን ያለች ምትናገር።

10 ሰዎችን ሁሉ አንድ ቦታ ምትሰበስብ እሳት ትከሰታለች ሰዎች ከሷ የሸሹ አንድ ቦታ ይሰበሰባሉ። አላህም አንድት ምርጥ ንፋስ ይልካል በ ላኢላሀ ኢለሏህ ያመነውን ሁሉ ነፍስ ምትወስድ የሆነች የአላህ የሆነን ነገር ሁሉ ምትወስድ የሆነች!! ሙእሚኖች እንዳለ ያልቃሉ በአሽራሮች በክፉ ከሃዲዎች ላይ ቂያማ ትቆማለሽ። የዛኔ የዱንያ ነገር ያበቃለታል።

ጌታችን ሆይ የተውበት በርህ ሳይዘጋ በፊት እውነተኛ ተውባን ስጠን።

أرسل كرسالة
شارك على صفحتي
شارك في المجموعة
لا يمكن الترجمة

━┈የጥበብ ጫፍ ┅━

አንድ የሁዳዊ ወደ ሩቅ ሀገር እይተጓዘ ሳለ በመሀል የሙስሊሞች ሀገር ይደርሳል።

ያው እንደምታውቁት ይሁዳ ሁሌም ሸር እንዳሰበ ነው።

እናም፦"እዚህ ከተማ ገብቼ ዑለማኦችን ማደናገር አለብኝ" ብሎ ያስባል።

ከዚያም ከተማዋን ሊገባ ሲል አንድ እረኛ ያጋጥመውና በሱ ሊጀምር ወሰነ እና እንዲህ በማለት ጨወታ ጀመረ፦"እኛ ሙስሊሞች እኮ ቁርአን ለመሀፈዝ በጣም እየተቸገርን ነው።

አንደኛ፦30 ጁዝ ነው በዝቷል።

ሁለተኛ፦አንቀፆችም በጣም ብዙ ናቸው።

ሶስተኛው እና አስቸጋሪው ፦ ቁርአን ውስጥ ድግምግሞሽ አለ።

ስለዚህ ለምን የተደጋገሙ አንቀፆችን አንሰርዝም? ምክንያቱም የቃላት መደጋገም ነው እንጂ ምንም አይደለም።

ድግምግሞሹን ከሰረዝን መሀፈዙም ይቀለናል።"

የሁዳው ይሄን ሁሉ ሲያወራ እረኛው በፅሞና ያዳምጠው ነበር።

ከዚያም እረኛው ቀና አለና፦"ንግግርህ በጣም ደስ ይላል አሪፍ ሀሳብ ነው።" አለው።

የሁዳው ደስታው ወደር አጣ ነገር ግን ድብቅ ሴራው እንዳይታወቅበት ደስታውን ደበቀው።

እረኛውም እንዲህ በማለት ንግግሩን ቀጠለ፦

"አንድ ጥያቄ አለኝ።

ባንተ የሰውነት አካል ውስጥ ድግምግሞሽ የለም?

ለምሳሌ፦ ሁለት እጅ

☞ሁለት አይን

☞ሁለት እግር

☞ሁለት ጆሮ.....

ታዲያ ሰውነትህ ቀለል እንዲልልህ አንድ አንዱን ለምን አትቆርጥም? ያው ድግምግሞሽ ነው እንጂ እኮ ምንም አይደለም"

ይሄን ሲለው የሁዳው ደነገጠ።ፊቱን አጨፍግጎ፦ "የእረኛዎቻቸው መልስ እንዲህ ከሆነ የዑለማኦቻቸው መልስ እንዴት ሊሆን ነው?" እያለ ከተማዋን ትቶ አለ

أرسل كرسالة
شارك على صفحتي
شارك في المجموعة
abu fadil قام بمشاركة
لا يمكن الترجمة

❓ሙስሊሞች ምንም አያዉቁም ሞኝ የዋህ ናቸዉ ብለዉ ይጠራጠራሉ ነዉ አዎ የዋህ ነን ነገረረ ግን ሁሉንም ነገር አላህ ያሳዉቀናል እናቅ አለን

ይሄንን ፎቶ አያቹታ በዲህ ልያታልሉ ይሞክር አሉ

ይህ የፔፕሲ ፋብሪካ ምን እዳደረገ ሲከስር አደለም ፊሊስጤን ብሎሊጥፍ #የአቡ_ኡበይዳ_ፎቶ_ሊስሉበት_ይችላሉ??

https://t.me/alshems_alshems_ale

አንታለልም

ኮካ ኮላ እን ፔፕሲን አትጠቀሙ እስራኤልን ሚደግፈ ነገር በሙሉ አትጠቀሙ ፎስቡክ እራሱ እረ ተቆጥረዉ አያልቁም አትጠቀሙ

image
أرسل كرسالة
شارك على صفحتي
شارك في المجموعة