UMMA TOKEN INVESTOR

About me

ሞት

Translation is not possible.

… ተፈቃሪያችን [ﷺ] ከመካ መውጣታቸው በተሰማ ጊዜ ሙስሊሞች በሚንቀለቀል ናፍቆት መጠባበቅ ጀመሩ። ህፃናት ሳይቀሩ "የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እየመጡ ነው!" እያሉ በጉጉት ይጠባበቃሉ።

ሰዎች በየቀኑ በጠዋት ማልደው ወደ ኮረብታማው የመዲና ዳር በመውጣት ዙርያ ገባውን ሲከታተሉ ይውላሉ። የቀትሩ ሀሩር ሲጠናባቸው ወደ ቤታቸው ይመለሳሉ። የናፈቁትን ነብይ ለማቀፍ፤ በርሱ ሰማይ ለመጠለል፤ በርሱ መሬት ለመሳፈር፤ በርሱ ሳንባ ለመተንፈስ፤ በርሱ መንገድ ለመኖር፤ ለርሱ ህይወት ለመሞት።…

በአንዱ ቀን ለረዥም ሰዓታት ሲጠባበቁ ከዋሉ በኋላ ወደ ቤት ተመለሱ። ልክ በቤታቸው ሲጠለሉ አንድ አይሁድ በዳገቱ ላይ ሆኖ የሚጠባበቀውን የግል ጉዳይ ለማየት ሲያማትር ከሩቅ ሲሪብዶውን እየገለጠ የሚገሰግስ ነጭ ለባሽ ጀመዓ ተመለከተ። የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እና ባልደረቦቻቸው ነበሩ።…

አይሁዱ ነፍሱን መቆጣጠር አቃተው። ከፍ ባለ ድምፅ «ዐረቦች ሆይ?! እድላችሁ መጣ! የምትጠብቁት [እድላችሁ] መጣ!» አለ።

መዲና በተክቢራ ተናወጠች! የሰማ ሁሉ ተወዳጁን [ﷺ] ለመቀበል ወደ መሸኛዋ ዐቀበት (ሰኒየቱል‐ወዳዕ) ተመመ!

አላሁ አክበር እያለ!

ጦለዐል በድሩ እያለ!…

አንዳንድ የታሪክ ሰዎች የሂጅራው ተዓምር የተከሰተው በብሩሁ ረቢዕ ነው ይላሉ!

አዎን! ረቢዕ ባለ ገድ ነው! እድለኛ ነው! ስሙም ብርሃን ነው! ፍካት ነው! ልምላሜ ነው! ድምቀት ነው! «ዕድላችንን» ያገኘንበት ወር ነው! ከርሳቸው በመለስ ሌላ እድል አንሻም! ሐቢብ [ﷺ] በቂ ናቸው!

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
utheirsif sirage Сhanged his profile picture
7 month
Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
utheirsif sirage Сhanged his profile picture
7 month
Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group