UMMA TOKEN INVESTOR

About me

የቂያማ ማብሰርያ ጡሩንባው ተነፍቶ የሰው ዘር በሙሉ ለዘመናት ከተጋደመበት ቀብር ውስጥ እንደ በረሀ አንበጣ እየተርመሰመሰ በመውጣት ላይ ነው። ሁሉም ከቀብሩ ወጥቶ ለዘመናት ተከናንቦት የቆየውን አዋራ እያራገፈ ሂሳብ ወደሚደረግበት ሜዳ እርቃኑን ሁኖ በመላእክት እየተነዳ ከትርምሱ መሀል ይንጋጋል። በዚህ መሀል

Qumuqta qilghuchi yo'q.

የቂያማ ማብሰርያ ጡሩንባው ተነፍቶ የሰው ዘር በሙሉ ለዘመናት ከተጋደመበት

ቀብር ውስጥ እንደ በረሀ አንበጣ እየተርመሰመሰ በመውጣት ላይ ነው።

ሁሉም ከቀብሩ ወጥቶ ለዘመናት ተከናንቦት የቆየውን አዋራ እያራገፈ ሂሳብ

ወደሚደረግበት ሜዳ እርቃኑን ሁኖ በመላእክት እየተነዳ ከትርምሱ መሀል

ይንጋጋል።

በዚህ መሀል የተወሰኑ ሰዎች ከትርምሱ ገንጠል ብለው የሒሳብ ሜዳውን እና

የሲራጥ ድልድዩን ትተው ወደ ጀነት በአቋራጭ ያለ ከልካይ ያመራሉ።

የአደም ዘር በሙሉ በፀሀዩ ሀሩር እና በገዛ ላባቸው እየተጥለቀለቁ

እየተተረማመሱ ባሉበት ሁኔታ እኚህ ውሱን ሰዎች ጀነት ደጃፍ ላይ ቁመው

ያንኳኳሉ።

ሪድዋን የጀነት ግዛት ሹም ነው፦‹‹እነ ማን ናችሁ? ሂሳብም ሆነ ሚዛን

አልተደረጋችሁም፤ እንዴት እዚህ መጣችሁ? ወደ ጀነት እንዴት ልትገቡ ነው?››

ሲል ይጠይቃቸዋል።

እነሱም ይሉታል፦‹‹ሪድዋን ሆይ! እኛ ለሒሳብም ሆነ ለሚዛን አንሰለፍም፤ ቁርአን

ላይ ስለኛ አላነበብክምን?››

ሪድዋንም ይጠይቃል፦‹‹ምን ተብሎ ነው የተፃፈው?››

እነሱም ሲመልሱለት፦‹‹ታጋሾቹ ምንዳቸውን የሚሰጡት ያለ ግምት ነው›› ሱረቱ

ዙመር

ይጠይቃቸዋል፦‹‹ትዕግስታችሁ ምን ያህል ነበር?››

እነሱም ሲመልሱለት፦‹‹ እኛ በዱንያ ህይወታችን ስንበደል እንታገስ ነበር፣

ድንበር ሲታለፍብንም ይቅር እንል ነበር፣ ሀፅያትም በፈፀምን ግዜም ማርታን

እንለምን ነበር፣ ፈተና በመጣብን ግዜም እንታገስ ነበር፣ ጌታችን ፀጋ በዋለልን

ግዜም እናመሰግን ነበር›› ይሉታል።

የጀነት ግዛት ሹምም፦‹‹እናንተ የማትፈሩ እና የማታዝኑ ስትሆኑ ጀነትንም

በሰላም ግቧት›› ብሎ በክብር ያስገባቸዋል።

ምንጭ፦

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Qumuqta qilghuchi yo'q.

አልሃምዱሊላህ

Send as a message
Share on my page
Share in the group
umma1697875511 Сhanged his profile picture
7 month
Qumuqta qilghuchi yo'q.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group