Translation is not possible.
#የበጐ #ተግባራት #መንገዶች #በርካታ #ስለመሆናቸው
 
#ክፍል_12
 
#ሐዲሥ 13 / 128
 
አቡ ሁረይራ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕከተኛ (ሶ.ዐ.ወ)፦ “በተሟላ ሁኔታ ዉዱእ ያደረገ፥ ከዚያም ወደ ጁሙዐህ ሶላት የመጣና (የሚነገረውን) በፀጥታ ያደመጠ በሁለቱ ጁሙዓዎች መካከልና የተጨማሪ ሦሥት ቀናት ወንጀሎቹ ይማሩለታል። ጠጠር የነካካ፥ (ለሚነገረው ነገር ሙሉ ትኩረት ያልሰጠ) ረብ የለሽ ተግባር ፈጽሟል።” (ሙስሊም ዘግበውታል)
 
ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች
 
→ ዉዱእን በተሟላ መልኩ መፈጸምና ጁሙዐን ወቅቱን ጠብቆ መስገድ የሚያስገኘው ትሩፋት።
 
1/ የጁሙዐህ ሶላት እያንዳንዱ ለአቅመ-አዳም በደረሰ ሙስሊም ላይ ግዴታ ነው። መስጊድ ውስጥ በጀማዓ እንጅ አይሰገድም።
2/ ጁሙዐ ሶላት የአስር ቀናት ጥቃቅን ወንጀሎችን ያስምራል።
3/ በጁሙዐ ሶላት ወቅት ኹጥባ በሚነገርበት ሰዓት በፀጥታ ማዳመጥ ግዲታ (ዋጂብ) ነው።
 
Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio
 
ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group