Translation is not possible.
#የበጐ #ተግባራት #መንገዶች #በርካታ #ስለመሆናቸው
 
#ክፍል_11
 
አላህ እንዲህ ብሏል፦
"...ከበጐ ሥራ የምትሠሩትን ሁሉ አላህ ያውቀዋል፤..." አል በቀራህ፡ 197"
 
#ሐዲሥ 13 / 127
 
ነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) ተከታዩን መናገራቸውን አቡ ሁረይራ (ረ.ዐ) አስተላልፈዋል፦ “መንገድ ላይ ሙስሊሞችን ያስቸግር የነበረን ዛፍ በመቁረጡ ሰበብ ጀንነት ውስጥ ሲዘዋወር አንድን ሰውዬ ተመልክቻለሁ።” (ሙስሊም ዘግበውታል)
በሌላ ዘገባ ደግሞ፦
“አንድ ሰው መንገድ ላይ በነበረ አንድ የዛፍ ዝንጣፊ አጠገብ አለፈ። “በአላህ ይሁንብኝ! ይህንን ሙስሊሞችን እንዳያስቸግር አስወግደዋለሁ” አለ። (በዚሁ ድርጊቱ) ጀንነት እንዲገባ ተደረገ” የሚል ተወስቷል።
 
በሌላ የሐዲስ ዘገባ እንደተወሳው፦
“ሰውየው በአንድ መንገድ በመጓዝ ላይ እያለ የሾህ ዝንጣፊ ያገኛል። ከመንገዱ ያስወግዳዋል። አላህ ይህንኑ መልካም ተግባሩን ተቀበለው። ምህረትንም ለገሰው።”
 
ከሐዲሡ የምንማረው ቁምነገር
 
፨ ከመንገድ ላይ ሰዎችን የሚያውክን ነገር የማስወገድ ትሩፋት፤ ሙስሊሞችን የሚጠቅምና ከጉዳት የሚከላከልን ተግባር የመከወን ጠቀሜታ።
 
Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio
 
ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group