Translation is not possible.
#አላህን_መፍራት
#ክፍል_1
አላህ እንዲህ ብሏል፦
(وَإِيَّـٰىَ فَٱرْهَبُونِ ﴿٤٠﴾)
"እኔንም ብቻ ፍሩ።" (አል_በቀራህ፡ 40)
#ሐዲሥ 50 / 397
የእውነተኞች ሁሉ እውነተኛ የሆኑት የአላህ መልዕክተኛ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ሲሉ ነግረውናል በማለት ኢብኑ መስዑድ (ረ.ዐ) አስተላልፈዋል ፦ "ከእናንተ አንዳችሁ የሚፈጠርበት ነገር ከእናቱ ሆድ ውስጥ ለአርባ ቀናት (የዘር) ፈሳሽ ሆኖ ይቆያል። ከዚያም ለተመሳሳይ ጊዜ የረጋ ደም ይሆናል። ከዚያም ለተመሳሳይ ጊዜ የተላመጠ ሥጋ ይሆናል። ከዚያም መላኢካ ተልኮ ነፍስ ይዘራበታል። (መላኢካ) አራት ነገሮች ይታዘዛል። ሲሳዩን፣ የሚሞትበትን ወቅት፣ ሥራውንና እድለቢስ (ሸቂይ) ወይም እድለኛ (ሰዒድ) መሆኑን (እንዲጽፍ)። ከርሱ ውጭ ሌላ አምላክ በሌላው (አምላክ) እምላለሁ! ከእናንተ አንዳችሁ በርሱና በጀነት መካከል አንድ ክንድ ያክል ርቀት እስኪቀረው ድረስ የጀነት ሰዎችን ሥራ ሲሠራ ይቆያል። (ትንሽ ሲቀረው) የተጻፈበት ይቀድመውና የእሳት ሰዎችን ሥራ በመሥራት እሳት ይገባል። ከእናንተ አንዳችሁ የእሳት ሰዎችን ሥራ ሲሠራ ይቆይና (ሊገባበት) አንዲት ክንድ ሲቀረው የተጻፈው ቀድሞት የጀነት ሰዎችን ሥራ በመሥራት ጀነት ይገባል።" (ቡኻሪና ሙስሊም)
ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች
1/ በቀዷ ቀደር _መልካምም ሆነ ክፉ_ ሁሉም ነገር ከአላህ እንደሆነ ማመን ያሻል።
2/ ሐዲሡ ወደ መልካም ሥራ ሰዎች እንዲሽቀዳደሙና በርሱው እንዲዘወትሩ ያነሳሳል።
3/ የሰዎች ስኬታማነት የሚለካው በፍጻሜያቸው ነው። እናም በተሠሩት መልካም ሥራ መኮፈስ መዝናናት የሚቻልበት ሁኔታ የለም።
4/ አንድ መልካም ሥራ የሠራ ሰው ንጹሕ እንደሆነ ሊያቆየው ይገባል። በክፉ ሥራ ሊበክለው አይገባም።
5/ ሁሌም በአላህ መታገዝ፣ ፍጻሜ እንዲያምር አላህን መጠየቅ፥ ክፉ ፍጻሜን መፍራትና ከርሱ በአላህ መጠበቅ ያስፈልጋል።
Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio
ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group