UMMA TOKEN INVESTOR

About me

يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا اتَّقُوا اللَّهَ وَلْتَنظُرْ نَفْسٌ مَّا قَدَّمَتْ لِغَدٍ ۖ وَاتَّقُوا اللَّهَ ۚ إِنَّ اللَّهَ خَبِيرٌ بِمَا تَعْمَلُونَ

Translation is not possible.

▣ ተውበት ላደረጉ አሏህ ይምራል!

۞ قُلْ يَا عِبَادِيَ الَّذِينَ أَسْرَفُوا عَلَىٰ أَنفُسِهِمْ لَا تَقْنَطُوا مِن رَّحْمَةِ اللَّهِ ۚ إِنَّ اللَّهَ يَغْفِرُ الذُّنُوبَ جَمِيعًا ۚ إِنَّهُ هُوَ الْغَفُورُ الرَّحِيمُ

በላቸው «እናንተ በነፍሶቻችሁ ላይ ድንበር ያለፋችሁ ባሮቼ ሆይ! ከአላህ እዝነት ተስፋ አትቁረጡ፡፡ አላህ ኃጢኣቶችን በመላ ይምራልና፡፡ እነሆ እርሱ መሓሪው አዛኙ ነውና፡፡

📗 ቁርኣን ሱራ አዝ\'ዙመር 39:53

ታላቁ ተንታኝ ኢብኑ ከሲር ረሂመሁሏህ እንዲህ አሉ:-

በዚህ በተከበረችው አንቀፅ ለሁሉም አማፂያን ከከሃዲም ሌሎችንም ወደ ፀፀት (ተውበት) እና መመለስ ጥሪ አለበት እንዲሁም አሏህ ወንጀልን ሁሉ ለተፀፀተና ከእርሷ ለተመለሰ ወንጀሏ ምንም ያህል ብትሆን ምንም ያህል ብትበዛ እንደ ባህር አረፋ እንኳ ብትሆን እንደሚምር ይገልፃል።

ይህች አንቀፅ ያለ ፀፀት (ተውበት) መተርጎም ትክክል አይሆንም ምክንያቱም ከሽርክ ላልተፀፀተ ከእርሱ ይቅር አይባልምና።

📗 ተፍሲር ኢብኑ ከሲር 4/75

إِنَّ اللَّهَ لَا يَغْفِرُ أَن يُشْرَكَ بِهِ وَيَغْفِرُ مَا دُونَ ذَٰلِكَ لِمَن يَشَاءُ ۚ وَمَن يُشْرِكْ بِاللَّهِ فَقَدِ افْتَرَىٰ إِثْمًا عَظِيمًا

አላህ በእርሱ ማጋራትን በፍጹም አይምርም፡፡ ከዚህ ሌላ ያለውንም (ኀጢአት) ለሚሻው ሰው ይምራል፡፡ በአላህም የሚያጋራ ሰው ታላቅን ኀጢአት በእርግጥ ቀጠፈ፡፡

📗 ቁርኣን ሱራ አን\'ኒሳእ 4:48

የሙፈሲሮች ኢማም አጥ\'ጠበሪይ እንዲህ አሉ:-

አሏህ በእሱ ላይ ማጋራትና መካድ ላልተፀፀተ አይምርም ከእዚህ ውጭ ላለው ለፈለገው ከወንጀልና ከሀጢአት ሰዎች ይምራል።

📗 ተፍሲር አጥ\'ጠበሪይ 4/128

ይህንን አንቀፅ በማስመልከት ኢብኑ ከሲር እንዲህ አሉ:-

إِنَّ اللَّهَ لَا يَغْفِرُ أَن يُشْرَكَ بِهِ

አላህ በእርሱ ማጋራትን በፍጹም አይምርም ማለትም በእርሱ ላይ አጋሪ ሆኖ ለተገናኘው ባሪያው አይምርም።

وَيَغْفِرُ مَا دُونَ ذَٰلِكَ

ከዚህ ሌላ ያለውንም (ኀጢአት) ይምራል ማለትም ከወንጀሎች

لِمَن يَشَاءُ

ለሚሻው ሰው ይምራል ማለትም ከባሮቹ

📗 ተፍሲር ኢብኑ ከሲር 1/701

إِنَّمَا التَّوْبَةُ عَلَى اللَّهِ لِلَّذِينَ يَعْمَلُونَ السُّوءَ بِجَهَالَةٍ ثُمَّ يَتُوبُونَ مِن قَرِيبٍ فَأُولَٰئِكَ يَتُوبُ اللَّهُ عَلَيْهِمْ ۗ وَكَانَ اللَّهُ عَلِيمًا حَكِيمًا

ጸጸትን መቀበል በአላህ ላይ የሚገባው ለእነዚያ ኀጢአትን በስህተት ለሚሠሩና ከዚያም ከቅርብ ጊዜ ለሚጸጸቱት ብቻ ነው፡፡ እነዚያንም አላህ በእነርሱ ላይ ጸጸትን ይቀበላል፡፡ አላህም ዐዋቂ ጥበበኛ ነው፡፡

📗 ቁርኣን ሱራ አን\'ኒሳእ 4:17

https://t.me/Wku_ms_Official_Channel/

Telegram: Contact @Wku_ms_Official_Channel

Telegram: Contact @Wku_ms_Official_Channel

ይህ ቻናል ትክክለኛው የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሲሆን፣ በቻናሉም፦ ➲ ሙስሊም ተማሪዎችን የተመለከቱ መረጃዎች ➲ በዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች መስጂድ ስለሚደረጉ ሀይማኖታዊ እንቅስቃሴዎች ለምሳሌ ➩ የዳዕዋ ፕሮግራም ➪ የቂርአት እንቅስቃሴ ➪ ሌሎችም ዝግጅቶች ሲኖሩ የሚለቀቁ ይሆናል በአላህ ፍቃድ። @Wku_ibnuabbas_bot https://t.me/Wku_ms_Official_Channe
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

☞የአሹራ ፃም ደረጃዎች

☞ይበልጥ የተወደደው የአሹራ አፃፃም

«ኢብኑ ኡሰይሚን አላህ ይዘንለትና እንዲህ ብሏል።»

📝የአሹራ ፃም አራት ደረጃዎች አሉት።

√ የመጀመርያውና ዋናው ደረጃ

« ይህም የሚሆነው ዘጠነኛው፣ አስረኛውና አስራ አንደኛው ቀን መፃም ነው።

☞ እነዚህ ሶስት ቀናቶች በተከታታይ መፃም ከሁሉም የተሻለና ትልቁ ደረጃም ነው። በዚህ ላይ የሚጠቁም መረጃ መቷል። ኢማሙ አህመድ ሙስነዳቸው ላይ እንዳሰፈረቱ የአላህ መልእክተኛ (ከአሹራ በፊትና በኋላ በመፃም አይሁዶችን ተቃረኗቸው) ብለዋል።

⁍አንድ ሰው እነዚህን ቀናቶች ከፃመ በየወሩ ሶስት ቀን መፃም የሚያስገኘውን ትልቅ ትሩፋትንም ያገኛል።

√ ሁለተኛው ደረጃ

ይህም ዘጠነኛውና አስረኛውን ቀን መፃም ነው።

የአላህ መልእክተኛም ይህን አስመልክቶ አይሁዶች አስረኛውን ቀን ብቻ ነው የሚፃሙት ሲባሉ፦ አይሁዶችን መፃረር ይወዱ ነበርና {ቀጣይ አመት አላህ ካኖረን ዘጠነኛውንም ጨምረን እንፃማለን ብለው ነበርና}። ይህ ማድረግ ደሞ ሁሉንም ካፊሮች መፃረርም ጭምር ነው።

√ ሶስተኛው ደረጃ

⁍ አስረኛውና አስራ አንደኛው ቀን መፃም ነው።

√ አራተኛውና የመጨረሻው ደረጃ

☞ይህም አስረኛውን ቀን ብቻ መፃም ነው።

«ስረኛውን ቀን ብቻ ነጥሎ መፃም በተመለከተ ከፊል ኡለማዎች የተፈቀደ ነው ሲሉ ከፊሎቹ ደሞ የተጠላ ነው ብለዋል።»

👉ከመረጃ አንፃር ይጠላል የሚለው ጠንካራ ስለሆነ ከዚህ ጭቅጭቅ ለመውጣት ሲባል ከአሹራው ቀን በፊት አንድ ቀን ማስቀደም ወይም ከአሹራ ቀን በኋላ አንድ ቀን ማስከተል ያስፈልጋል።

[سلسلة لقاء الباب المفتوح (٩٥)]

∽ማሳሰቢያ‼️

〰〰〰〰〰

አንዳንድ ኡለማዎች አስረኛውን ቀን ብቻውን መፃም ይጠላል ማለታቸው፦ ፃሙ ተቀባይነት የለውም ወይም ውድቅ ነው ማለት እንዳልሆነ መረዳት ያስፈልጋል።

=

http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru

Telegram: Contact @Sadik_Ibnu_Heyru

Telegram: Contact @Sadik_Ibnu_Heyru

➡️ በቻናላችን የሚሰጡ የትምህርት አይነቶች ➲የአቂዳ ኪታቦች ➲የፊቅህ ግንዛቤዎች ➲የሱና ኡለማዎች ፈትዋ ➲ወቅታዊ ምክሮች ➲የቁርአን ቂርአትና ሌሎችም http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ስለ ሴቶች ፈተና አስፈሪ ታሪክ

ታሪኩን የሚነግሩን አብዳህ ኢብኑ አብዱልሃኪም እንዲህ ይላሉ

“በድብቅ ወደ ሮማውያን ምድር ዘመትን። በዘመቻውም ላይ አንድ ወጣት ተጎዳኝቶን ነበር። ከኛ ውስጥ ከሱ የተሻለ ቁርአን የሚቀራ ከሱ የተሻለ የፊቅህ እውቀት የነበረው ከሱ የተሻለ ስለ ፈራኢድ የሚያውቅ አልነበረም። ቀኑን ፁሞ የሚውል ለሊቱን ሲሰግድ የሚያድር ኣቢድ ወጣት ነበር። የኛ ሰራዊት በአንድ ምሽግ ውስጥ ለቀናት ሰፍረ።

ይህ ወጣት ሁል ግዜ ለሊቱ ሲመሽ ለመስገድ ጌታውን ለማናገር ከምሽጉ ይወጣል። አንዲት ክርስቲያን ሴትም ከምሽጉ ጀርባ ሁና ትመለከተው የሚቀራውንም ቁርአን ታደምጥ ነበር።

ከእለታት በአንዱ ቀን ወጣቱ ከእኛ ዞር ብሎ ወደ ምሽጉ አቅራቢያ ሌላ እንዳንሰፍርበት በተከለከልነው ምሽግ ውስጥ ሰፈረ። ወደልጅቷም ይመለከት ጀመር እሷም ከምሽጉ ጀርባ ሁና ትመለከተው ያዘች። ልጅቷ አላህ ከፈጠራቸው ፍጥረቶች እጅግ ውብ ነበረች። ከማማሯ የተነሳ ፀሀይ በፊቷ ላይ የምትጓዝ ትመስላለች።

ወደ ምሽጉ ቀረብ ብሎ ያስተውላት ጀመር።ከጠላት ምሽግ ቅርብ ከመሆኑ የተነሳ የጠላት ቀስቶች እንዳይወድቁበት ሰጋን። በየግዜ ይህን ያደርግ ጀመር። ይህንን ነገር ማዘውተር ባበዛ ግዜ ፍቅር ላይ ወደቀ ራሱን መቆጣጠር እስከማይችል ድረስ ልቡ በሷላይ ተንጠለጠለ። አንድ ቀን ራሱን አደጋ ላይ ጥሎ በሮማን ቋንቋ “ በምን መንገድ ነው የማገኝሽ?” ሲል ጠየቃት። እሷም “ ክርስቲያን ስትሆን” ስትል መለሰችለት። ልጁም \"በአላህ እጠበቃለሁ!” ብሏት ጥሏት ሄደ። ከጥቂት ቀናት በኋላ ተመልሶ ወደሷ በመምጣት እንዲህ አላት “ በሶላቴ ውስጥ እና ቁርአንን በማነብ ግዜ ባንቺ ተጠምጃለሁ (ሃሳቤ ያለው ካንቺ ጋር ነው)። በምን መንገድ ነው ላገኝሽ የምችለው?”። እሷም “ ክርስቲያን ሁን በሩንም እንከፍትልሃለን ከምሽጉም እናስገባሃለን እኔም ያንተ እሆናለሁ” አለችው። (አሁን ግን በአላህ እጠበቃለሁ የሚለውን ቃል አንደበቱ መናገር አልቻለም። ልቡ በፍቅሯ ታውሯል አንደበቱ ተሳስሯል። ፍቅር በሚሉት ሃይል ተማርኳል። የምትለውን ከመቀበል ውጭ ምርጫ አልነበረውም።)

ያለችውን አድርጎ ወደ ምሽጋቸው ገባ፤ ከእርሷ ጋር ሆኖ ከፊትለፊቱ መስቀሉን ለብሶ ካልሆነ በቀር አናያቸውም።\"

አስከትለውም እንዲህ ይላሉ “ዘመቻችንን በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ሆነን አጠናቀቅን። ከመካከላችን ያለው ሰው ሁሉ ያንን ወጣት ከወገቡ ተወልዶ ክርስትናን እንደተቀበለ አድርጎ ያየው ነበር።

ከግዜያት በኋላ በሌላ ቡድን ተመልሰን መጣን። በአጠገቡ አለፍን። ከክርስትያኖች ጋር ከምሽጉ በላይ ይታያል። እገሌ ሆይ የምትቀራው ቁርአን ምን ሰራ?! ያሁሉ መልካም ስራ ስገደት ፆምህ ወዴት ገባ ምን ሰራ?” ብለን ጠየቅነው።

እሱም “እወቁ እኔ ቁርአንን ሙሉ በሙሉ እረስቻለሁ። በፍፁም ከዚህች አንቀፅ ውጭ

رُّبَمَا يَوَدُّ الَّذِينَ كَفَرُوا لَوْ كَانُوا مُسْلِمِينَ

ذَرْهُمْ يَأْكُلُوا وَيَتَمَتَّعُوا وَيُلْهِهِمُ الْأَمَلُ ۖ فَسَوْفَ يَعْلَمُونَ

{እነዚያ የካዱት (በትንሣኤ ቀን) ሙስሊሞች በኾኑ ኖሩ በብዛት ይመኛሉ፡፡

ተዋቸው ይብሉ፤ ይጠቀሙም፡፡ ተስፋም ያዘናጋቸው፡፡ በእርግጥም (መጥፎ ፍጻሜያቸውን) ያውቃሉ፡፡} በፍፁም ምንንም ከቁርአን አንቀፅ አላስታውስም። ” አለን። እኛም እንዲህ አልን“ ይህ ሰው በእውቀት ላይ አላህ ያጠመመው ሰው ነው።”

ከዛም አብዳህ ቢን አብዱረሂም እንዲህ ይላሉ፡- “እኛ ልጁን አናግረን ዘወር እንዳልን ብዙም ሳንሄድ አንድ ጥቁር ነገር ወደኛ ሲመጣ ተመለከትን። ያቺ ሴት ነበረች ወደ ካሃድያን ምሽግ ልጁን ያስገባችው ሴት። ወደሷም ዞርንና “ይህ ልጅ ከእምነቱ ፈተንሽው (ከሃዲ አደረግሽው) አልናት።

እሷም “በአላህ እምላለሁ፣ (የሚያነበው ቁርአን ማርኮኝ) የሚያነበውን ለመስማት ብቻ ነው ወደሱ ስመለከት የነበረው፣ የሚያነበውን (ቁርአን) ለመስማት ስል ነበር ያገባሁት። እሱ ግን የሚያነበውን ሁሉ በአንድ ጊዜ ረሳው፣ ስለዚህም ከእሱ ምንም ሳልጠቀም ቀረሁ። አሁን ከእናንተ ውስጥ እሱ ሲያነበው የነበረውን (ቁርአን) የሚያነብ አለን?” ብላ ጠየቀችን ለእርሷም ተነበበላት። እርሷም “ወላሂ ይህ ያ በእውነት ስሰማው የነበረው ነገር ነው” አለች።

እስልምናን ተቀብላ ከእነርሱ (ከሙስሊሙ ሰራዊት) ጋር ሙስሊም ሆና ተመለሰች እርሱም ምሽጉ ላይ መስቀሉን ለብሶ ከክርስትያኖች ጋር ኖረ።

ልቦናን እንዳሻው የሚጠለባብጥ ጌታ ጥራት ይገባው።

የታሪኩ ምንጭ

ኢብኑል ጀውዚ \"ታሪኩል ሙሉክ ወ ኡመሚሂም\" ከሚለው ኪታባቸው

አቡበክር አል-በይሃቂ \"ሹአቡል ኢማን\" ከሚለው ኪታባቸው

🖊 Abdulkerim Husen

https://t.me/Amirposts/

Telegram: Contact @Amirposts

Telegram: Contact @Amirposts

‏قال الإمام الأوزاعي رحمه الله «عليك بآثار من سلف وإن رفضك الناس، وإياك ورأي الرجال وإن زخرفوه بالقول؛ فإن الأمر ينجلي وأنت منه على طريق مستقيم».
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

የነብዩ ﷺ ሚስቶች - ረዲየላ፞ሁ ዐንሁን።

1. ዓኢሻ ቢንት አቢ በክር

2. ሰውዳህ ቢንት ዘምዐህ

3. መይሙና ቢንቲል ሐሪስ

4. ዘይነብ ቢንት ኹዘይማህ

5. ኸዲጃ ቢንት ኹወይሊድ

6. ዘይነብ ቢንት ጀህሽ አልሂላሊያ

7. ሐፍሷ ቢንት ዑመር ብኒል ኸጧብ

8. ሶፊያህ ቢንት ሑየይ ብኒ አኽጦብ

9. ጁወይሪያ ቢንቲል ሐሪሥ አልኹዛዒያ

10. ኡሙ ሰለማህ ሂንድ ቢንት አቢ ኡመያ

11. ኡሙ ሐቢባህ ረምላ ቢንት አቢ ሱፊያን

https://t.me/MOhamedAljawi

Telegram: Contact @MOhamedAljawi

Telegram: Contact @MOhamedAljawi

على مِنهاجِ النُّبوَّة
Send as a message
Share on my page
Share in the group