🔺ዑለማዎቻችንን እንተዋወቅ
#ክፍል4
~~~
ኢማሙ አሕመድ፡ (164-241 ዓ.ሂ)
«ኢማሙ አህሊ ሱንና ወል ጀመዓ»
ሙሉ ስማቸው አቡ ዓብዱልሏህ አሕመድ ኢብኑ ሙሐመድ ኢብኑ ሐምበል ሸይባኒ አል ማሩዚ ይባላሉ።
ኢማሙ አሕመድ በ164 ዓ.ሂ በባጝዳድ ተወለዱ።
ባጝዳድ በዚያን ጊዜ በበኑ አባስ ስርወ መንግስት ግዛት ስር ስለነበረች፣
አይነተኛዋ የሙስሊሞች ከተማ ነበረች።
ኢማሙ አሕመድ አባታቸውን ገና የሶስት አመት ህጻን ሳሉ በሞት አጥተዋል።
የዘር ግንዳቸው ከነብዩልሏህ ኢብራሂም ዓለይሂ ስ-ሰላም ጋር የሚያያዝ ንጹህ ዓረብ ናቸው።
ኢማሙ አሕመድ ቁርአንን ገና በለጋ እድሚያቸው ነው የሐፈዙት።
✍️በ180 ዓ.ሂ የ16 አመት ታዳጊ በነበሩበት ጊዜ፣
የኢማሙ አቡ ሐኒፋ ታዋቂ ተማሪ በሆኑት በኢማም አቡ ዩሱፍ ላይ ሐዲሥን መማር ጀመሩ።
ከኢማም አቡ ዩሱፍ ጋርም ለሶስት አመታት ያክል በመቆየት ብዙ ነገሮችን ተምረዋል።
ኢማሙ አሕመድ በባጝዳድ ከብዙ ዑለማዎች ላይ ከተማሩ በኋላ፣
የሐዲሥ እውቀት አድማሳቸውን ለማስፋት ወደ ኩፋ፣ በስራ፣ መካ፣ መዲና፣ የመን፣ ሶሪያ እና ወደ አልጀዚራ አቀኑ።
ከመቶ በላይ ከሆኑ ሸይኾች ጋር ከተገናኙ በኋላም፣
ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሆኑ ሐዲሦችን የማሰባሰብ ስራ ጀመሩ።
👉በ187 ዓ.ሂ ኢማሙ አሕመድ ለመጀመሪያ ጊዜ ኢማሙ ሻፊዒይን በመካ አገኟቸው።
በኋላም ኢማሙ ሻፊዒይ ወደ ባጝዳድ ሲሄዱ፣
ኢማሙ አሕመድም አብረው ተቀላቅለው ከኢማሙ ሻፊዒይ ላይ የሒዲሥ እውቀታቸውን ይበልጥ አዳበሩት፣ አመጠቁት።
ኢማሙ ሻኢዒይ በኢማሙ አሕመድ የሐዲሥና የሱንና እውቀት ላይ በጣም ተስፋ ጣሉ።
እጅጉን ተገረሙባቸው፣ አድናቆትንም ቸሯቸው።
👉ጊዜው 204 ዓ.ሂ ነበር፤
ኢማሙ አሕመድ በአርባ አመታቸው ማስተማርን ጀመሩ።
ወደ 5,000 ያክል ተማሪዎች ይከታተሏቸዋል።
500 ያክሉ ደግሞ በየቀኑ ፊት ለፊታቸው በመገኘት ከርሳቸው ትምህርት የሚወስዱ ናቸው።
ኢማም ቡኻሪ፣ ኢማም ሙስሊም፣ ኢማም ቲርሚዚይ
ከእነዚህ የእለት ተእለት ተማሪዎች መካከል ዋነኞቹ ናቸው።
✍️ኢማሙ አሕመድን ለ አመታት ተፋፍሞ ይበልጥ የጎላ ፈተና አጋጠማቸው።
ይሄውም <<ቁርአን ፍጡር ነው።>> የሚለው የሙዕተዚላዎች አስተሳሰብ ነበር።
በሰአቱ የነበሩት የበኑ አባስ መሪዎች አል መዕሙንና አል ሙዕተሶም፤
እንደ ኢማሙ አሕመድ ያሉ ዑለማዎችን የሙዕተዚላዎችን እርዕዮት ተቀበሉ ብለው ጫና አደረጉባቸው፣ አስገደዷቸው።
ይህ ጊዜ ለኢማሙ አሕመድና ለመሰል የዘመናቸው ዑለማዎች እጅጉን ፈታኝ ነበር።
ኢማሙ አሕመድ ግን ፈተናውን እንደምንም ተወጡት።
በኋላም አል ሙተወኪል የበኑ አባስን የመሪነት ስልጣን ተቆናጠጠ።
ለኢማሙም እውቅና ሰጠ፣ እርሳቸውም ተመቻቸው።
ማስተማራቸውንም ቀጠሉ።
✍️ከአስተማሪዎቹ መካከል፥
=================
#አቡ ዩሱፍ (ያዕቁብ ኢብኑ ኢብራሂም አል አንሷሪ)
#ኢማሙ ሻፊዒይ
#ሑሻይም ኢብኑ በሽር
#ኢብራሂም ኢብኑ ሰዒድ
#ያሕያ ኢብኑ ሰዒድ
#አቡ ሙሐመድ ስ ኡፍያን ኢብኑ ዑየይናህ
#ኢማም የዚድ ኢብኑ ሃሩን
#ኢማም ዋቂዕ ኢብኑል ጀራህ
እና ሌሎችም።
✍️ከተማሪዎቻቸው መካከል፥
================
#ኢማም ቡኻሪ
#ኢማም ሙስሊም
#ኢማም ቲርሚዚይ
#አቡ ዳውድ ሱለይማን
#አቡ ዙርራዓህ
#ዓብደልሏህ ኢብኑ አሕመድ ኢብኑ ሐንበል (ልጃቸው)
#ሷሊሕ ኢብኑ አሕመድ ኢብኑ ሐንበል (ልጃቸው)
#አቡል ሐሰን ዓሊ ኢብኑ ሙሐመድ አል መውሩዲ
#አቡበከር አል አሥረም
#ሐምበል ኢብኑ ኢስሐቅ
#አቡል ቃሲም አል በጘዊይ
እና ሌሎችም።
✍️ከመጽሃፍቶቻቸው መካከል፥
==================
ኢማሙ አሕመድ ብዙ ድርሳናቶች አሏቸው።
ከነዚህም ውስጥ፦
📚ሙስነድ ኢማም አሕመድ (ከ30, 000 ገደማ በላይ ሐዲሦችን ያቀፈ ነው።)
📚አስ-ሱንና
📚ኡሱሉ ሱንና
📚ኪታቡል ዒለል ወመዕሪፈቲ ሪጃል
📚ኪታቡል መናሲክ
📚ኪታቡ ዙህድ
📚ኪታቡል ኢማን
📚ኪታቡል መሳኢል
📚ኪታቡል አሽሪባ
📚ኪታቡል ፈራኢድ
📚ኪታቡ ር-ረድ
📚ኪታብ ፈዷኢሉ ሶሐባ
📚ኪታብ ጦዓቱ ርረሱል
እና ሌሎችም።
✍️የዑለማዎች ውዳሴ፦
=============
✔️ኢማሙ ሻፊዒይ ስለ ኢማሙ አሕመድ እንዲህ ይላሉ፦
"ከባጝዳድ ለቅቄ ስወጣ፣
ከአሕመድ ኢብኑ ሐምበል የበለጠ
በጎ ስነ ምግባር ያለው፣ አዋቂ፣ ምሁር ማንንም ትቼ አልወጣሁም።"
"እንዲህ ብለዋል፦
አሕመድ ኢብኑ ሐምበል በብዙ የእውቀት መስኮች ተቀዳሚ ምሁር ነው።
በፊዊህ፣ በሐዲሥ፣ በቁርአን፣ በተቅዋ እና በሱንና እውቀት።"
✔️ልጃቸው ዓብደልሏህ አቡ ዙርራዓህ እንዲህ ሲለኝ ሰምቻለሁ ይላል፦
"አባትህ (አሕመድ) አንድ ሚሊዮን ሐዲሥ ሸምዷል።"
✔️ዓሊ አልመዲኒ እንዲህ ይላል፥
አላህ ይህንን ዲን በሪዳ ዕለት (ሰዎች ነብያችን የሞቱ ጊዜ ወደ ኩፍር በተመለሱበት ዕለት) በአቡበከር ሲዲቅ አጠንክሮታል።
አሁንም በሚህናህ ዕለት (ሰዎች ቁርአን ፍጡር ነው ብላችሁ በሉ ተብለው በተገደዱበት ዕለት) ይህን ዲን በአሕመድ ኢብኑ ሐምበል አጠንክሮታል።"
✔️አቡ ሠውር እንዲህ ይላሉ፥
"አሕመድ ከሱፍያነ ሠውሪ የበለጠ አዋቂ ነበር።"
✔️የሕያ ኢብኑ መዒን እንዲህ ይላል፦
"ሰዎች እንደ አሕመድ ኢብኑ ሐምበል እንድንሆን ይፈልጋሉ።
በአላህ ይሁንብኝ፣ መቼም አንሆን።
እንኳን እንደ አሕመድ ያለን ጠንካሮች ልንሆን ቀርቶ፣
የአሕመድን ፈለግ ለመከተል እንኳ ጠንካራ አንሆንም።"
✔️ዓብዱል ማሊክ አልመይሙኒ እንዲህ ይላል፦
"አይኖች ከአሕመድ ኢብኑ ሐምበል የበለጠ ሰው አይተው አያውቁም።"
✔️ቁተይባህ ኢብኑ ሰዒድ እንዲህ ይላል፦
"ሱፍያን ሠውሪ በሞተ ጊዜ፣ ተቅዋም አብሮ ሞተ።
ሻፊዒይ በሞቱ ጊዜ ለሱንና በትክክል እጅ መስጠት አብሮ ሞተ።
አሕመድ የሞቱ ጊዜ፣ ቢዲዓ ተፈጠረ።"
ሌሎችም ውዳሴዎች አሉ።
✍️ህልፈታቸው፥
============
ኢማሙ አሕመድ ለዘጠኝ ቀናት ያክል ታመው፣
እለተ ጁሙዓ ረቢዓል አወል 12, 241 ዓ.ሂ በ77 አመታቸው ከዚህች አለም በሞት ተለዩ።
የቀብር ስነ ስርአታቸውም በባጝዳድ ተፈጽሟል።
በዚህ ዕለትም አንድ ሚሊዮን ያክል ሰዎች በሶላተል ጀናዛ ላይ ተሳትፈዋል።
በአጠቃላይ በአለም ደረጃም ከሁለት ሚሊዮን አምስት መቶ ሺህ በላይ ሰዎች ሰግደዋል።
አንዳንድ ዘገባዎች እንደሚያሳይቱም 20, 000 ያክል አይሁዳውያንና ክርስቲያኖች በዚህ ዕለት እስልምናን ተቀብለዋል።
አላሁ አክበር‼️
ኢማሙ አሕመድ ታላቅ ፈርጥ ናቸው።
ኢማሙ አሕመድ ከአራቱ ታዋቂ የፊቂህ ጠበብቶች ውስጥ አንዱ ናቸው።
የሐናቢላ (ሐንበልያ) መዝሃብ መሰረትም ናቸው።
ረሒመሁልሏህ ራሕመተን ዋሲዓ።
((ለበለጠ መረጃ፥
ሲየሩል አዕላም አንኑበላዕ፣ ቮሊዩም 11
ተዝኪረቱል ኹፋዝ (የኢማሙ ዘሃቢይን)
እና ሌሎችንም ተመልከቱ።
https://t.me/WATESiMU
🔺ዑለማዎቻችንን እንተዋወቅ
~~~
ኢማሙ አሕመድ፡ (164-241 ዓ.ሂ)
«ኢማሙ አህሊ ሱንና ወል ጀመዓ»
ሙሉ ስማቸው አቡ ዓብዱልሏህ አሕመድ ኢብኑ ሙሐመድ ኢብኑ ሐምበል ሸይባኒ አል ማሩዚ ይባላሉ።
ኢማሙ አሕመድ በ164 ዓ.ሂ በባጝዳድ ተወለዱ።
ባጝዳድ በዚያን ጊዜ በበኑ አባስ ስርወ መንግስት ግዛት ስር ስለነበረች፣
አይነተኛዋ የሙስሊሞች ከተማ ነበረች።
ኢማሙ አሕመድ አባታቸውን ገና የሶስት አመት ህጻን ሳሉ በሞት አጥተዋል።
የዘር ግንዳቸው ከነብዩልሏህ ኢብራሂም ዓለይሂ ስ-ሰላም ጋር የሚያያዝ ንጹህ ዓረብ ናቸው።
ኢማሙ አሕመድ ቁርአንን ገና በለጋ እድሚያቸው ነው የሐፈዙት።
✍️በ180 ዓ.ሂ የ16 አመት ታዳጊ በነበሩበት ጊዜ፣
የኢማሙ አቡ ሐኒፋ ታዋቂ ተማሪ በሆኑት በኢማም አቡ ዩሱፍ ላይ ሐዲሥን መማር ጀመሩ።
ከኢማም አቡ ዩሱፍ ጋርም ለሶስት አመታት ያክል በመቆየት ብዙ ነገሮችን ተምረዋል።
ኢማሙ አሕመድ በባጝዳድ ከብዙ ዑለማዎች ላይ ከተማሩ በኋላ፣
የሐዲሥ እውቀት አድማሳቸውን ለማስፋት ወደ ኩፋ፣ በስራ፣ መካ፣ መዲና፣ የመን፣ ሶሪያ እና ወደ አልጀዚራ አቀኑ።
ከመቶ በላይ ከሆኑ ሸይኾች ጋር ከተገናኙ በኋላም፣
ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሆኑ ሐዲሦችን የማሰባሰብ ስራ ጀመሩ።
👉በ187 ዓ.ሂ ኢማሙ አሕመድ ለመጀመሪያ ጊዜ ኢማሙ ሻፊዒይን በመካ አገኟቸው።
በኋላም ኢማሙ ሻፊዒይ ወደ ባጝዳድ ሲሄዱ፣
ኢማሙ አሕመድም አብረው ተቀላቅለው ከኢማሙ ሻፊዒይ ላይ የሒዲሥ እውቀታቸውን ይበልጥ አዳበሩት፣ አመጠቁት።
ኢማሙ ሻኢዒይ በኢማሙ አሕመድ የሐዲሥና የሱንና እውቀት ላይ በጣም ተስፋ ጣሉ።
እጅጉን ተገረሙባቸው፣ አድናቆትንም ቸሯቸው።
👉ጊዜው 204 ዓ.ሂ ነበር፤
ኢማሙ አሕመድ በአርባ አመታቸው ማስተማርን ጀመሩ።
ወደ 5,000 ያክል ተማሪዎች ይከታተሏቸዋል።
500 ያክሉ ደግሞ በየቀኑ ፊት ለፊታቸው በመገኘት ከርሳቸው ትምህርት የሚወስዱ ናቸው።
ኢማም ቡኻሪ፣ ኢማም ሙስሊም፣ ኢማም ቲርሚዚይ
ከእነዚህ የእለት ተእለት ተማሪዎች መካከል ዋነኞቹ ናቸው።
✍️ኢማሙ አሕመድን ለ አመታት ተፋፍሞ ይበልጥ የጎላ ፈተና አጋጠማቸው።
ይሄውም <<ቁርአን ፍጡር ነው።>> የሚለው የሙዕተዚላዎች አስተሳሰብ ነበር።
በሰአቱ የነበሩት የበኑ አባስ መሪዎች አል መዕሙንና አል ሙዕተሶም፤
እንደ ኢማሙ አሕመድ ያሉ ዑለማዎችን የሙዕተዚላዎችን እርዕዮት ተቀበሉ ብለው ጫና አደረጉባቸው፣ አስገደዷቸው።
ይህ ጊዜ ለኢማሙ አሕመድና ለመሰል የዘመናቸው ዑለማዎች እጅጉን ፈታኝ ነበር።
ኢማሙ አሕመድ ግን ፈተናውን እንደምንም ተወጡት።
በኋላም አል ሙተወኪል የበኑ አባስን የመሪነት ስልጣን ተቆናጠጠ።
ለኢማሙም እውቅና ሰጠ፣ እርሳቸውም ተመቻቸው።
ማስተማራቸውንም ቀጠሉ።
✍️ከአስተማሪዎቹ መካከል፥
=================
#አቡ ዩሱፍ (ያዕቁብ ኢብኑ ኢብራሂም አል አንሷሪ)
#ኢማሙ ሻፊዒይ
#ሑሻይም ኢብኑ በሽር
#ኢብራሂም ኢብኑ ሰዒድ
#ያሕያ ኢብኑ ሰዒድ
#አቡ ሙሐመድ ስ ኡፍያን ኢብኑ ዑየይናህ
#ኢማም የዚድ ኢብኑ ሃሩን
#ኢማም ዋቂዕ ኢብኑል ጀራህ
እና ሌሎችም።
✍️ከተማሪዎቻቸው መካከል፥
================
#ኢማም ቡኻሪ
#ኢማም ሙስሊም
#ኢማም ቲርሚዚይ
#አቡ ዳውድ ሱለይማን
#አቡ ዙርራዓህ
#ዓብደልሏህ ኢብኑ አሕመድ ኢብኑ ሐንበል (ልጃቸው)
#ሷሊሕ ኢብኑ አሕመድ ኢብኑ ሐንበል (ልጃቸው)
#አቡል ሐሰን ዓሊ ኢብኑ ሙሐመድ አል መውሩዲ
#አቡበከር አል አሥረም
#ሐምበል ኢብኑ ኢስሐቅ
#አቡል ቃሲም አል በጘዊይ
እና ሌሎችም።
✍️ከመጽሃፍቶቻቸው መካከል፥
==================
ኢማሙ አሕመድ ብዙ ድርሳናቶች አሏቸው።
ከነዚህም ውስጥ፦
📚ሙስነድ ኢማም አሕመድ (ከ30, 000 ገደማ በላይ ሐዲሦችን ያቀፈ ነው።)
📚አስ-ሱንና
📚ኡሱሉ ሱንና
📚ኪታቡል ዒለል ወመዕሪፈቲ ሪጃል
📚ኪታቡል መናሲክ
📚ኪታቡ ዙህድ
📚ኪታቡል ኢማን
📚ኪታቡል መሳኢል
📚ኪታቡል አሽሪባ
📚ኪታቡል ፈራኢድ
📚ኪታቡ ር-ረድ
📚ኪታብ ፈዷኢሉ ሶሐባ
📚ኪታብ ጦዓቱ ርረሱል
እና ሌሎችም።
✍️የዑለማዎች ውዳሴ፦
=============
✔️ኢማሙ ሻፊዒይ ስለ ኢማሙ አሕመድ እንዲህ ይላሉ፦
"ከባጝዳድ ለቅቄ ስወጣ፣
ከአሕመድ ኢብኑ ሐምበል የበለጠ
በጎ ስነ ምግባር ያለው፣ አዋቂ፣ ምሁር ማንንም ትቼ አልወጣሁም።"
"እንዲህ ብለዋል፦
አሕመድ ኢብኑ ሐምበል በብዙ የእውቀት መስኮች ተቀዳሚ ምሁር ነው።
በፊዊህ፣ በሐዲሥ፣ በቁርአን፣ በተቅዋ እና በሱንና እውቀት።"
✔️ልጃቸው ዓብደልሏህ አቡ ዙርራዓህ እንዲህ ሲለኝ ሰምቻለሁ ይላል፦
"አባትህ (አሕመድ) አንድ ሚሊዮን ሐዲሥ ሸምዷል።"
✔️ዓሊ አልመዲኒ እንዲህ ይላል፥
አላህ ይህንን ዲን በሪዳ ዕለት (ሰዎች ነብያችን የሞቱ ጊዜ ወደ ኩፍር በተመለሱበት ዕለት) በአቡበከር ሲዲቅ አጠንክሮታል።
አሁንም በሚህናህ ዕለት (ሰዎች ቁርአን ፍጡር ነው ብላችሁ በሉ ተብለው በተገደዱበት ዕለት) ይህን ዲን በአሕመድ ኢብኑ ሐምበል አጠንክሮታል።"
✔️አቡ ሠውር እንዲህ ይላሉ፥
"አሕመድ ከሱፍያነ ሠውሪ የበለጠ አዋቂ ነበር።"
✔️የሕያ ኢብኑ መዒን እንዲህ ይላል፦
"ሰዎች እንደ አሕመድ ኢብኑ ሐምበል እንድንሆን ይፈልጋሉ።
በአላህ ይሁንብኝ፣ መቼም አንሆን።
እንኳን እንደ አሕመድ ያለን ጠንካሮች ልንሆን ቀርቶ፣
የአሕመድን ፈለግ ለመከተል እንኳ ጠንካራ አንሆንም።"
✔️ዓብዱል ማሊክ አልመይሙኒ እንዲህ ይላል፦
"አይኖች ከአሕመድ ኢብኑ ሐምበል የበለጠ ሰው አይተው አያውቁም።"
✔️ቁተይባህ ኢብኑ ሰዒድ እንዲህ ይላል፦
"ሱፍያን ሠውሪ በሞተ ጊዜ፣ ተቅዋም አብሮ ሞተ።
ሻፊዒይ በሞቱ ጊዜ ለሱንና በትክክል እጅ መስጠት አብሮ ሞተ።
አሕመድ የሞቱ ጊዜ፣ ቢዲዓ ተፈጠረ።"
ሌሎችም ውዳሴዎች አሉ።
✍️ህልፈታቸው፥
============
ኢማሙ አሕመድ ለዘጠኝ ቀናት ያክል ታመው፣
እለተ ጁሙዓ ረቢዓል አወል 12, 241 ዓ.ሂ በ77 አመታቸው ከዚህች አለም በሞት ተለዩ።
የቀብር ስነ ስርአታቸውም በባጝዳድ ተፈጽሟል።
በዚህ ዕለትም አንድ ሚሊዮን ያክል ሰዎች በሶላተል ጀናዛ ላይ ተሳትፈዋል።
በአጠቃላይ በአለም ደረጃም ከሁለት ሚሊዮን አምስት መቶ ሺህ በላይ ሰዎች ሰግደዋል።
አንዳንድ ዘገባዎች እንደሚያሳይቱም 20, 000 ያክል አይሁዳውያንና ክርስቲያኖች በዚህ ዕለት እስልምናን ተቀብለዋል።
አላሁ አክበር‼️
ኢማሙ አሕመድ ታላቅ ፈርጥ ናቸው።
ኢማሙ አሕመድ ከአራቱ ታዋቂ የፊቂህ ጠበብቶች ውስጥ አንዱ ናቸው።
የሐናቢላ (ሐንበልያ) መዝሃብ መሰረትም ናቸው።
ረሒመሁልሏህ ራሕመተን ዋሲዓ።
((ለበለጠ መረጃ፥
ሲየሩል አዕላም አንኑበላዕ፣ ቮሊዩም 11
ተዝኪረቱል ኹፋዝ (የኢማሙ ዘሃቢይን)
እና ሌሎችንም ተመልከቱ።
Comment
Share
Send as a message
Share on my page
Share in the group