🔺ዑለማዎቻችንን እንተዋወቅ‼️
#ክፍል3
~~~
#ኢማሙ ሻፊዒይ፡ (150-204 ዓ.ሂ)
ሙሉ ስማቸው አቡ ዓብዱልሏህ ሙሐመድ ኢብኑ ኢድሪስ ኢብኑ አባስ ኢብኑ ዑሥማን ሻፊዒይ ይባላሉ።
በ150 ዓ.ሂ በጋዛ (አስቃላን) በሃገረ ሶሪያ ተወለዱ።
የዘር ግንዳቸው ከቁረይሽ ጎሳ (ዓብዱል መናፍ) የተመዘዘ ሲሆን፣
ከነብዩ ሶለላሁ ዓለይሂ ወሰለም የዘር ግንድ ጋር ተያያዥነት ያላቸው ብቸኛው ኢማም ናቸው።
ሻፊዒይ አባታቸውን ያጡት ገና በለጋ እድሚያቸው ስለነበር፣
ያደጉት ከየመናዊቷ እናታቸው ጋር በከፋ ድህነት ውስጥ ሁነው ነው።
ገና የሰባት አመት ህጻን በነበሩ ጊዜ ቁርኣንን ሐፍዘዋል።
በአስራ ሶስት አመታቸው ደግሞ የኢማሙ ማሊክን "ሙወጦእ" ሐፍዘዋል።
በወቅቱ የመካ ሙፍቲ የነበሩት የሻፊዒይ ሸይኽ ሙስሊም ኢብኑ ኻሊድ ለሻፊዒይ ፈቅደውላቸው በአስራ አምስት አመታቸው ፈተዋ መስጠት ጀምረዋል።
✍️ ሻፊዒይ ለእውቀት ካላቸው ጉጉት የተነሳ ከመካ ወጣ አሉ።
በሃያ አመታቸው ገደማ ወደ መዲና በማቅናት ከኢማሙ ማሊክ ላይ ለስምንት ወራት ያክል ተምረዋል።
ኢማሙ ማሊክም <<ሙወጦእን>> በለጋ እድሚያቸው በሐፈዙት በኢማሙ ሻፊዒይ ይደነቁ ነበር።
የሻፊዒይን የእውቀት አቀባበልና የአረዳድ ፍጥነታቸውን በጣም ያደንቁት ነበር።
ኢማሙ ማሊክ ተማሪያቸውን ኢማሙ ሻፊዒይን እንዲህ ሲሉ ይገልጿቸዋል፥
"ወደኔ ለመማር ከመጡ ተማሪዎች ውስጥ እንደ ሙሐመድ ኢብኑ ኢድሪስ ሻፊዒይ ያለ ብሩህና አዋቂ አላየሁም።"
ሻፊዒይ ከስምንት ወራት ቆይታ በኋላ ወደ መካ ተመልሰዋል።
ከታላቁ ዓሊም ከሱፍያን ኢብኑ ዑየይናህ ላይም ተምረዋል።
ኢማሙ ሻፊዒይ ኢማሙ ማሊክንና ሱፍያን ኢብኑ ዑየይናህን በተመለከተ እንድህ ብለዋል፥
"ኢማሙ ማሊክና ሱፍያን ባይኖሩ ኑሮ፣
እውቀት በሒጃዝ ውስጥ አይቆይም ነበር።"
ሻፊዒይ ቁርኣንና ሐዲሥን ከ81 በላይ ከሆኑ ዓሊሞች ላይ ተምረዋል።
👉ሻፊዒይ በ34 አመታቸው ወደ ባጝዳድ አቀኑ።
እዚያም ለሶስት አመታት ያክል ከኢማም ሙሐመድ ላይ ተምረዋል።
ኢማሙ ሻፊዒይ ስለ ኢማም ሙሐመድ ሲናገሩ እንዲህ ይላሉ፦
"ከኢማም ሙሐመድ በላይ የአላህን ኪታብ አዋቂ የሆነ አንድንም አላውቅም።"
ኢማም ሙሐመድም ስለ ሻፊዒይ ሲናገሩ እንዲህ ይላሉ፥
"የፊቂህ (የእውቀት) በር ለህዝቦች ተዘግቶ ነበር፤
አላህ በሻፊዒይ ሰበብ ከፈተው።
ሻፊዒይ የዲኑ ሙጀዲድ (አዳሽ) ነው።"
ኢብኑ ራሓዊ <<ኢማሙ ሻፊዒይ እንደት በልጅነታቸው ይህን ሁሉ መፅሀፍ ሊሐፍዙ ቻሉ??>> ተብለው ተጠይቀው፥
"አላህ ሱብሐነሁ ወተዓላ በወጣትነታቸው ምጡቅና በሳል አስተሳሰብ ሰጥቷቸዋል" አሉ።
ኢማሙ ሻፊዒይ የሐነፍያንና የማሊኪያን ፊቂህ በማጥናት የራሳቸውን የሻፊዒያ ፊቂህ መሰረት ጥለዋል።
👉ኢማሙ ሻፊዒይ የኸሊፋውን ዑሥማን ኢብኑ አፋን ረዲየልሏሁ ዓንሁ የልጅ ልጅ ሐምዲያህ ቢንት ናፊን በመካ አግብተው ሶስት ልጆችን ወልደዋል።
ከነዚህም ውስጥ ሁለቱ ወንዶች ሲሆኑ ስማቸውም፥ ዑሥማንና ሐሳን ይባላሉ።
አንዷ ልጃቸው ሴት ስትሆን ስሟም ፋጢማ ትባላለች።
#ከአስተማሪዎቹ መካከል፥
===============
#ሙስሊም ኢብኑ ኻሊድ (በመካ)
#ሱፍያን ኢብኑ ዑየይናህ (በመካ)
#ኢብራሂም ኢብኑ የሕያህ (በመዲና)
#ኢማሙ ማሊክ ኢብኑ አነስ (በመዲና)
#ዋቂዕ ኢብኑል ጀራህ (በኩፋ)
#ሙሐመድ ኢብኑ ሐሳን (በበስራ)
#ሐማድ ኢብኑ ኡሳማህ (በኩፋ)
#ዓብዱል ወሃብ ኢብኑ ዓብዱል መጅድ (በበስራ)
እና ሌሎችም።
✍️ከተማሪዎቻቸው መካከል፥
================
#ኢማም አቡ የዕቁብ
#አቡ ኢብራሂም ኢስማዒል ኢብኑ ያሕያ
#ረቢዕ ኢብኑ ሱለይማን
#አቡ ዓሊ አለከራቢሲ
#ኢብራሂም ኢብኑ ኻሊድ
#ኢማሙ አሕመድ ኢብኑ ሐንበል (በጥቂቱ)
እና ሌሎችም።
📚ከመጽሃፍቶቻቸው መካከል፥
==================
ኢማሙ ሻፊዒይ ከመቶ በላይ የሚሆኑ ድርሳናቶች አሏቸው።
ከነዚህም ውስጥ፦
📚ኪታቡል "ኡም" (በጣም ታዋቂ ኪታባቸው ነው።)
📚አር-ሪሳላህ አልጀዲዳህ
📚ኪታቡል ሱነን
📚ኢኽቲላፉል ሐዲሥ
📚አሕካሙል ቁርኣን
📚ኢኽቲላፉል ሐዲሥ
📚ሲፈቱል አምር ወንነሂይ
📚አል ኢምላ
📚ኢብጣሉል ኢስቲሕሳን
📚ኢኽቲላፉል ኢራቂያኒ
📚ኪታቡል ሑጃህ
📚ኢኽቲላፉል ማሊክ ወሽሻፊዒይ
እና ሌሎችም።
✍️ህልፈታቸው፥
============
ኢማሙ ሻፊዒይ በመጨረሻም ወደ ግብጽ በማምራት ትንሽ ከቆዩ በኋላ፣
በድንገተኛ ህመም ምክንያት፣
እለተ ሐሙስ ከዒሻእ ሶላት በኋላ በወርሃ ረጀብ የመጨረሻው ቀን ሙተው ጁሙዓ በካይሮ በበኑ ዓብዱል ሐኪም ቫውልት መቃብር ተቀብረዋል።
አመቱም 204 ዓ.ሂ ነበር።
እድሚያቸው 54 አመት ነው።
ሻፊዒይ ከአራቱ ታዋቂ የፊቂህ ጠበብቶች ውስጥ አንዱ ናቸው።
ረሒመሁልሏህ ራሕመተን ዋሲዓ።
https://t.me/WATESiMU
🔺ዑለማዎቻችንን እንተዋወቅ‼️
~~~
#ኢማሙ ሻፊዒይ፡ (150-204 ዓ.ሂ)
ሙሉ ስማቸው አቡ ዓብዱልሏህ ሙሐመድ ኢብኑ ኢድሪስ ኢብኑ አባስ ኢብኑ ዑሥማን ሻፊዒይ ይባላሉ።
በ150 ዓ.ሂ በጋዛ (አስቃላን) በሃገረ ሶሪያ ተወለዱ።
የዘር ግንዳቸው ከቁረይሽ ጎሳ (ዓብዱል መናፍ) የተመዘዘ ሲሆን፣
ከነብዩ ሶለላሁ ዓለይሂ ወሰለም የዘር ግንድ ጋር ተያያዥነት ያላቸው ብቸኛው ኢማም ናቸው።
ሻፊዒይ አባታቸውን ያጡት ገና በለጋ እድሚያቸው ስለነበር፣
ያደጉት ከየመናዊቷ እናታቸው ጋር በከፋ ድህነት ውስጥ ሁነው ነው።
ገና የሰባት አመት ህጻን በነበሩ ጊዜ ቁርኣንን ሐፍዘዋል።
በአስራ ሶስት አመታቸው ደግሞ የኢማሙ ማሊክን "ሙወጦእ" ሐፍዘዋል።
በወቅቱ የመካ ሙፍቲ የነበሩት የሻፊዒይ ሸይኽ ሙስሊም ኢብኑ ኻሊድ ለሻፊዒይ ፈቅደውላቸው በአስራ አምስት አመታቸው ፈተዋ መስጠት ጀምረዋል።
✍️ ሻፊዒይ ለእውቀት ካላቸው ጉጉት የተነሳ ከመካ ወጣ አሉ።
በሃያ አመታቸው ገደማ ወደ መዲና በማቅናት ከኢማሙ ማሊክ ላይ ለስምንት ወራት ያክል ተምረዋል።
ኢማሙ ማሊክም <<ሙወጦእን>> በለጋ እድሚያቸው በሐፈዙት በኢማሙ ሻፊዒይ ይደነቁ ነበር።
የሻፊዒይን የእውቀት አቀባበልና የአረዳድ ፍጥነታቸውን በጣም ያደንቁት ነበር።
ኢማሙ ማሊክ ተማሪያቸውን ኢማሙ ሻፊዒይን እንዲህ ሲሉ ይገልጿቸዋል፥
"ወደኔ ለመማር ከመጡ ተማሪዎች ውስጥ እንደ ሙሐመድ ኢብኑ ኢድሪስ ሻፊዒይ ያለ ብሩህና አዋቂ አላየሁም።"
ሻፊዒይ ከስምንት ወራት ቆይታ በኋላ ወደ መካ ተመልሰዋል።
ከታላቁ ዓሊም ከሱፍያን ኢብኑ ዑየይናህ ላይም ተምረዋል።
ኢማሙ ሻፊዒይ ኢማሙ ማሊክንና ሱፍያን ኢብኑ ዑየይናህን በተመለከተ እንድህ ብለዋል፥
"ኢማሙ ማሊክና ሱፍያን ባይኖሩ ኑሮ፣
እውቀት በሒጃዝ ውስጥ አይቆይም ነበር።"
ሻፊዒይ ቁርኣንና ሐዲሥን ከ81 በላይ ከሆኑ ዓሊሞች ላይ ተምረዋል።
👉ሻፊዒይ በ34 አመታቸው ወደ ባጝዳድ አቀኑ።
እዚያም ለሶስት አመታት ያክል ከኢማም ሙሐመድ ላይ ተምረዋል።
ኢማሙ ሻፊዒይ ስለ ኢማም ሙሐመድ ሲናገሩ እንዲህ ይላሉ፦
"ከኢማም ሙሐመድ በላይ የአላህን ኪታብ አዋቂ የሆነ አንድንም አላውቅም።"
ኢማም ሙሐመድም ስለ ሻፊዒይ ሲናገሩ እንዲህ ይላሉ፥
"የፊቂህ (የእውቀት) በር ለህዝቦች ተዘግቶ ነበር፤
አላህ በሻፊዒይ ሰበብ ከፈተው።
ሻፊዒይ የዲኑ ሙጀዲድ (አዳሽ) ነው።"
ኢብኑ ራሓዊ <<ኢማሙ ሻፊዒይ እንደት በልጅነታቸው ይህን ሁሉ መፅሀፍ ሊሐፍዙ ቻሉ??>> ተብለው ተጠይቀው፥
"አላህ ሱብሐነሁ ወተዓላ በወጣትነታቸው ምጡቅና በሳል አስተሳሰብ ሰጥቷቸዋል" አሉ።
ኢማሙ ሻፊዒይ የሐነፍያንና የማሊኪያን ፊቂህ በማጥናት የራሳቸውን የሻፊዒያ ፊቂህ መሰረት ጥለዋል።
👉ኢማሙ ሻፊዒይ የኸሊፋውን ዑሥማን ኢብኑ አፋን ረዲየልሏሁ ዓንሁ የልጅ ልጅ ሐምዲያህ ቢንት ናፊን በመካ አግብተው ሶስት ልጆችን ወልደዋል።
ከነዚህም ውስጥ ሁለቱ ወንዶች ሲሆኑ ስማቸውም፥ ዑሥማንና ሐሳን ይባላሉ።
አንዷ ልጃቸው ሴት ስትሆን ስሟም ፋጢማ ትባላለች።
#ከአስተማሪዎቹ መካከል፥
===============
#ሙስሊም ኢብኑ ኻሊድ (በመካ)
#ሱፍያን ኢብኑ ዑየይናህ (በመካ)
#ኢብራሂም ኢብኑ የሕያህ (በመዲና)
#ኢማሙ ማሊክ ኢብኑ አነስ (በመዲና)
#ዋቂዕ ኢብኑል ጀራህ (በኩፋ)
#ሙሐመድ ኢብኑ ሐሳን (በበስራ)
#ሐማድ ኢብኑ ኡሳማህ (በኩፋ)
#ዓብዱል ወሃብ ኢብኑ ዓብዱል መጅድ (በበስራ)
እና ሌሎችም።
✍️ከተማሪዎቻቸው መካከል፥
================
#ኢማም አቡ የዕቁብ
#አቡ ኢብራሂም ኢስማዒል ኢብኑ ያሕያ
#ረቢዕ ኢብኑ ሱለይማን
#አቡ ዓሊ አለከራቢሲ
#ኢብራሂም ኢብኑ ኻሊድ
#ኢማሙ አሕመድ ኢብኑ ሐንበል (በጥቂቱ)
እና ሌሎችም።
📚ከመጽሃፍቶቻቸው መካከል፥
==================
ኢማሙ ሻፊዒይ ከመቶ በላይ የሚሆኑ ድርሳናቶች አሏቸው።
ከነዚህም ውስጥ፦
📚ኪታቡል "ኡም" (በጣም ታዋቂ ኪታባቸው ነው።)
📚አር-ሪሳላህ አልጀዲዳህ
📚ኪታቡል ሱነን
📚ኢኽቲላፉል ሐዲሥ
📚አሕካሙል ቁርኣን
📚ኢኽቲላፉል ሐዲሥ
📚ሲፈቱል አምር ወንነሂይ
📚አል ኢምላ
📚ኢብጣሉል ኢስቲሕሳን
📚ኢኽቲላፉል ኢራቂያኒ
📚ኪታቡል ሑጃህ
📚ኢኽቲላፉል ማሊክ ወሽሻፊዒይ
እና ሌሎችም።
✍️ህልፈታቸው፥
============
ኢማሙ ሻፊዒይ በመጨረሻም ወደ ግብጽ በማምራት ትንሽ ከቆዩ በኋላ፣
በድንገተኛ ህመም ምክንያት፣
እለተ ሐሙስ ከዒሻእ ሶላት በኋላ በወርሃ ረጀብ የመጨረሻው ቀን ሙተው ጁሙዓ በካይሮ በበኑ ዓብዱል ሐኪም ቫውልት መቃብር ተቀብረዋል።
አመቱም 204 ዓ.ሂ ነበር።
እድሚያቸው 54 አመት ነው።
ሻፊዒይ ከአራቱ ታዋቂ የፊቂህ ጠበብቶች ውስጥ አንዱ ናቸው።
ረሒመሁልሏህ ራሕመተን ዋሲዓ።
Comment
Share
Send as a message
Share on my page
Share in the group