Translation is not possible.
#የበጐ #ተግባራት #መንገዶች #በርካታ #ስለመሆናቸው
 
#ክፍል_14
 
#ሐዲሥ 13 / 130
 
የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) ተከታዩን መናገራቸውን አቡ ሁረይራ (ረ.ዐ) አስተላልፈዋል፦ “አምስት ወቅት ሶላቶች፥ ከጁሙዐህ እስከ ጁሙዐህ፥ ከአንዱ ረመዷን እስከ ሌላኛው ረመዷን በመካከላቸው ለሚፈጸሙ (ጥቃቅን) ወንጀሎች ማበሻዎች ናቸው፤ ታላላቅ ወንጀሎች እስካልተፈጸሙ ድረስ።” (ቡኻሪ ዘግበውታል)
 
ከሐዲሡ የምንማረው ቁምነገር
 
፨ እነኝህን ግዳጆች በአግባቡ መፈጸም ለጥቃቅን ወንጀሎች መሰረይ ምክንያት ሊሆን ይችላል፤ በአላህ እዝነት (ረሕመት) እና ትሩፋት፡፡ ሰውየው ታላላቅ ወንጀሎችን ካልፈጸመ ከወንጀል የጸዳ ይሆናል። ታላላቅና ታናናሽ ወንጀሎችን የፈጸመ ከሆነ ግን በታላላቅ ወንጀሎች ብቻ ይጠየቃል። ታላላቅ ወንጀሎችንም ቢሆን አላህ ያቀልለታል ተብሎም ይታሰባል። ግን እውነተኛ ተውበት የግድ አስፈላጊው ነው።
 
Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio
 
ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group