Çĕнĕ çулахне йывăçлăх
አንድ ሰው ነብኑን (ሶለላሁ አለይሂ ወሰልም) አንቱ የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ጌታዬን እንዴት አድርጌ ልጠይቀው (ልማፀነው)? ብሎ ሲጠይቃቸው እንዲህ በል አሉት፦
“አላህ ሆይ! ማረኝ፣ እዘንልኝ፣ ጤነኛ አድርገኝ፣ ሲሳይን ለግሰኝ”!!
▲ ይህ የዱንያና የአኺራ ጉዳዮችን ላንተ ጠቅልሎ ይዞልሃል።
#ሙስሊም_ዘግበውታል
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
እናም ተማሪዎች አርአያችን የአላህን መልዕክተኛ (ሶለላሁ አለይሂ ወሰልም) ናቸውና እኛም ሁሌም ይህንን ዱዓ እናድርግ። ጌታችንን ተናንሰን እንማፀነው‼️
ልብ ልንል የሚገባን ነገር ቢኖር:-
እኛ ጥረት እያደረግንም ሆነ ጥረት ካደረግን በኋላ መመካት ያለብን በጥረታችን ((በልፋታችን)) ሳይሆን በአላህ ነው። በአላህ በመመካት እሱ (አላህ) እንዲያሳካልን ሁሌም ልንለምነው ይገባል። «በአላህ ፍቃድ ይሳካልኛል፣ ጥሩ ውጤት አመጣለሁ» በማለት ንባባችንን አጠናክረን መቀጠል አለብን‼️
⭕️ አደራችሁን መልዕክቱን ለሁሉም ተማሪዎች አድርሱልኝ።
✍️ በናተው ወንድም ረሻድ ኢብኑ ሙዘሚል
image
Хыпар пек ярас
Ман тетелӗ питра пайлас
Ушкӑнта пайлас