#ሶላት_ውስጥ #ያለ_ምክንያት_መዟዟር_ስለመጠላቱ
#ሐዲሥ 341 / 1755
ዓኢሻ እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፦ የአላህ መልዕክተኛ ሶላት ውስጥ ስለመዘዋወር ጠይቄያቸው፦ “እርሱ ሰይጣን የሚፈጽመው ጠለፋ ነው” በማለት መለሱልኝ። (ቡኻሪ)
#ሐዲሥ 341 / 1756
አነስ እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል፦ “ሶላት ውስጥ መዟዟር ጥፋት ነውና። መዟዟርህ የግድ ከሆነ በሱንና እንጅ በግዴታ ሶላቶች መሆን የለበትም።” (ቲርሚዚ)
ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች
1/ ሶላት ውስጥ መዟዟር ይጠላል። ልቦና ከሶላት መዘናጋቱንና በሌላ ነገር ጠመዱን ያመለክታል። ለዚህም ነው ሰይጣን የሚፈጽመው ጠለፋ ነው የተባለው። ሰይጣን የሰጋጁን መዘናጋት ተጠቅሞ ስሜቱን ይሰርቀዋል። ወደ ሌላ አቅጣጫም ያዞረዋል።
2/ ሶላት ውስጥ መዟዟር ጥፋት ነውም ተብሏል። ዒባዳ ውስጥ አላህን ትቶ ለሰይጣን ጉትጎታ ጆሮ መስጠት በመሆኑ። በተጨማሪም የሚጠሉ ነገሮችን ማቃለልና ደጋግሞ መፈጸም ሐራም ላይ ሊጥል ይችላል። ለቅጣትም ያበቃል።
3/ መዟዟር ለአንዳች ምክንያት ወይም ችግር ከሆነ ግን አይጠላም።
4/ እስካሁን የተጠቀሰው ፊትን ብቻ ማዞርን በተመለከተ ነው። ደረትን ማዞር ግን ሐራም ነው። ሶላትንም ያበላሻል። ምክንያቱም ከሶላት መሠረታዊ መስፈርቶች ውስጥ አንዱ የሆነውን ወደ ቂብላ የመዞርን መስፈርት ስለሚያጠፋ ነው።
Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio
ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1
ዓኢሻ እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፦ የአላህ መልዕክተኛ ሶላት ውስጥ ስለመዘዋወር ጠይቄያቸው፦ “እርሱ ሰይጣን የሚፈጽመው ጠለፋ ነው” በማለት መለሱልኝ። (ቡኻሪ)
አነስ እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል፦ “ሶላት ውስጥ መዟዟር ጥፋት ነውና። መዟዟርህ የግድ ከሆነ በሱንና እንጅ በግዴታ ሶላቶች መሆን የለበትም።” (ቲርሚዚ)
ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች
1/ ሶላት ውስጥ መዟዟር ይጠላል። ልቦና ከሶላት መዘናጋቱንና በሌላ ነገር ጠመዱን ያመለክታል። ለዚህም ነው ሰይጣን የሚፈጽመው ጠለፋ ነው የተባለው። ሰይጣን የሰጋጁን መዘናጋት ተጠቅሞ ስሜቱን ይሰርቀዋል። ወደ ሌላ አቅጣጫም ያዞረዋል።
2/ ሶላት ውስጥ መዟዟር ጥፋት ነውም ተብሏል። ዒባዳ ውስጥ አላህን ትቶ ለሰይጣን ጉትጎታ ጆሮ መስጠት በመሆኑ። በተጨማሪም የሚጠሉ ነገሮችን ማቃለልና ደጋግሞ መፈጸም ሐራም ላይ ሊጥል ይችላል። ለቅጣትም ያበቃል።
3/ መዟዟር ለአንዳች ምክንያት ወይም ችግር ከሆነ ግን አይጠላም።
4/ እስካሁን የተጠቀሰው ፊትን ብቻ ማዞርን በተመለከተ ነው። ደረትን ማዞር ግን ሐራም ነው። ሶላትንም ያበላሻል። ምክንያቱም ከሶላት መሠረታዊ መስፈርቶች ውስጥ አንዱ የሆነውን ወደ ቂብላ የመዞርን መስፈርት ስለሚያጠፋ ነው።
Umma Life
ቴሌግራም/ telegram/