Translation is not possible.

📹 ላለፉት 4 ሰአታት በመቶዎች የሚቆጠሩ የእስራኤል ወታደሮች፣ ልዩ ሃይሎች እና የተጠባባቂ ሃይሎች በዌስት ባንክ የእስራኤላዊያን መኪና ተጠቅሞ ጥቃት ከፈፀመ አንድ የፍልስጤም ተቃውሞ ተዋጊ ጋር እየተዋጉ ነው።

ወደ ሆስፒታል የተወሰዱትን ሁለቱን ጨምሮ ቢያንስ 4 ሰዎች ቆስለዋል የሚል መረጃ ወጥቶ ነበር።

ሰራዊቱ ከ20 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በፍልስጤም አስተዳደር መቀመጫ ራማላህ ከተማ አካባቢው የጦር ሄሊኮፕተር ተጠቅሟል።

የዕብራይስጥ ቻናል 12 ተዋጊው የተገደለው ከበርካታ የእስራኢል ወታደሮች እና ሄሊኮፕተሮች ጋር ሲፋረም ቆይቶ ከራማላ በስተ ምዕራብ በሚሳኤል ከተመታ በኋላ ነው ብሏል።

የዲዮት አህሮኖት በበኩሉ በምዕራባዊ ራማላህ በተካሄደው ኦፕሬሽን የተጎዱ ሰዎች ቁጥር ወደ 7 ከፍ ያለ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ 3ቱ በጠና ሁኔታ ላይ ናቸው ብሏል።

ድርጊቱ የተካሄደው በራማላ ሰሜናዊ ምዕራብ በምትገኘው በካፍር ኒማ መንደር በቢኒያሚን አውራጃ ውስጥ በሚገኘው ዶሌቭ ሰፈር ነው።

ሌሎች ወቅታዊ መረጃዎችም በቴሌግራም እየተለቀቁ ስለሆነ @islaminformer ላይ ጆይን አድርጉ

በሙስሊሙ ዓለም የተፈጠሩ ሁሉንም አዳዲስ መረጃዎች በተለይም በወቅታዊ የፍልስጤም ጉዳይ እውነተኛ እና ሚዛናዊ መረጃ ለማግኘት የሙሐመድ ትውልድ ገፅን ፎሎው ያድርጉ

6 views
Send as a message
Share on my page
Share in the group