Translation is not possible.

አጅግ አስቀያሚ ኢ-ስነምግባራዊ ድርጊት!

በየትኛው መመዘኛ ቢሆን እኚህን አባት በዚህ ደረጃ ማመናጨቅና መደብደብ ተገቢነት የለውም። መርካቶ ውስጥ ሌባ ጋር ስትተናነቅ አይቶ ባላየ የሚያልፍ የፀጥታ አካል እንዲህ አይነት አፀያፊ ተግባር ላይ ሲገኝ የጸጥታ አካላት ኃላፊነታቸው የህዝብን ሰላምና ደህንነት ከማስጠበቅ ይልቅ አማራጭ በማጣት እና በግዴለሽነት እየሰሩ መሆናቸውን ያሳያል፡፡ ብልሹ ስነ ምግባራቸውን ያላስተካከሉ ሞራልና ርኅራኄ የሚባል ነገር ያልሠራባቸው ወንበዴ የፖሊስ አካላት በእንዲህ አይነት ቀና ብሎ ለማየት እንኳ በማያስደፍሩ አባቶች ላይ የሚፈፅሙት ውንድብና የጸጥታ አካሉን ስም የሚያቆሽሽ ነው።

ሙስሊሞችን በመጥላት መሰረታዊ ችግር ላይ የተዘፈቁ የፀጥታ አካላት ሳይረፍድ ወደ መንገድ የማይገቡ ከሆን ሀገሪቱን ከማንም በፊት የሚያጠፏት እንዲህ አይነት ህዝብ ይጠብቃሉ ተብለው የሚጠበቁ ተራ አስተሳሰብ የያዙ ግለሰቦች ናቸው፡፡ ይህ የፖሊስ አባል በህግ ቁጥጥር ስር ውሎ ተገቢው ተመጣጣኝና አስተማሪ እርምጃ ሊወሰድ ይገባል፡፡

ሙስሊሙ ማህበረሰብ ጠንካራ መጅሊስ እንደሌለው ግልፅ ነው ግን እስኪ አንዳንዴ እንዲህ አይነት አስነዋሪ ተግባር ሲፈፀም እያያችሁ ምላሽ ባለመስጠት ሙስሊሙን የበለጠ ተጋላጭ አታድርጉት ቢያንስ ጉዳዩን ተከታተሉ ተበዳይን አበረታቱ ወንጀለኛው ላይ ክስ መስርቱ ፍትህ እንደሌለ እናውቃለን አብሽሩ፡፡

በሙስሊሙ ዓለም የተፈጠሩ ሁሉንም አዳዲስ መረጃዎች በተለይም በወቅታዊ የፍልስጤም ጉዳይ እውነተኛ እና ሚዛናዊ መረጃ ለማግኘት የሙሐመድ ትውልድ ገፅን ፎሎው ያድርጉ

6 views
Send as a message
Share on my page
Share in the group