Наган дахаан йохтахам.

ሃማስ የእስራኤልን ጥያቄ ውድቅ አደረገ!

የግብፅ ባለስልጣናት እንደገለፁት እስራኤል የፍልስጤም እስረኞችን በመልቀቅ በሐማስ የተያዙ ዜጎቿን ለማስፈታት በዚህም የሁለት ወር የተኩስ አቁም ለማድረግ ከስምምነት ላይ ለመድረስ እስራኤል ያቀረበችውን ሀሳብ ሐማስ ውድቅ አድርጎታል፡፡

ሐማስ በምላሹ መሪዎቹ ጋዛን ለቀው እንደማይወጡ እና እስራኤል ሙሉ በሙሉ ከጋዛ ለቃ እንድትወጣ እንዲሁም ፍልስጤማውያን በአስቸኳይ ወደ ቤታቸው እንዲመለሱ ቅድመ ሁኔታ አስቀምጧል፡፡

የእስራኤል ገዥ አካል ጦርነቱን ሙሉ በሙሉ ለማቆምም ሆነ 6,000 የሚሆኑ የፍልስጤም እስረኞችን ለመፍታት እንደማይስማማ የገለፀ ሲሆን ግን በርካታ ፍልስጤማዊያን እስረኞችን ለመልቀቅ መስማማቱን አስታውቋል።

በሙስሊሙ ዓለም የተፈጠሩ ሁሉንም አዳዲስ መረጃዎች በተለይም በወቅታዊ የፍልስጤም ጉዳይ እውነተኛ እና ሚዛናዊ መረጃ ለማግኘት የሙሐመድ ትውልድ ገፅን ፎሎው ያድርጉ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group