Çeviri imkansız.

ስለጋዛ ልንገራችሁ

መረጃ ቁጥር 1

👉 እስራኤል በጋዛ የሚገኘውን ጦሯን ማስወጣት ጀምራለች ። ዛሬና ትላንትም በሺህ የሚቆጠር እግረኛ ሜካናይዝድና አየር ወለድ ጦሯ ጋዛን ለቆ ወጥቷል ።በእግር ጦር እያደረገቺው ያለው ጦርነት ከፍተኛ የሰው ሀይሏን እየጨረሰባት ያለውና ወታደራዊ ተሽከርካሪዎቿ በከፍተኛ ሁኔታ የወደሙባት እስራኤል በእግር ጦር መቀጠሉ ከፍተኛ ኪሳራን እያከናነባት ይገኛል ። እናም ጦሯን ለማስወጣት ተገዳለች ። በአሁኑ ሰአት በርካታ የጦር ክፍሎቿ ጋዛን እየለቀቁ ሲሆን የአየር ድብደባዋን ግን አጠናክራ ቀጥላለች !

👉 ሀማስ ሰሞኑን በእስራኤል ላይ የሚያደርሰው ምት ከእስከዛሬውም እያየለ ከመሄዱም አልፎ ለመጀመሪያ ጊዜ በ SA-47 ሚሳኤሉ የእስራኤልን ሄሊኮፕተሮችና የጦር ጀቶች ኢላማ ውስጥ ማስገባቱ ከፍተኛ ድንጋጤን በእስራኤል ዘንድ ፈጥሯል ። ጨርሶ ይወድማል ይጠፋል ያሉት ሀማስ እንኳንስ ሊጠፋና እንኳንስ ሊዳከምና እስከዛሬ ያልተጠቀማቸውን መሳሪያዎች ሁሉ መጠቀም መጀመሩ እስራኤልን አሳስቧል ።ሀማስ እያሸነፈ ነው ብቻ ሳይሆን አሸንፏል የሚሉት ተንታኞች ብዙ ናቸው !! ሀማስ በዚህ ሁለት ቀን እያነጣጠረ በፈፀማቸው ጥቃቶች በርካታ የእስራኤል ወታደሮችን ደምስሷል ።

👉 34 የሞሳድ ሰላዮች በቱርክ በቁጥጥር ስር ውለዋል ። እስራኤል በቱርክ በኳታርና በሊባኖስ ያሉ የሀማስ አመራሮችን አድኜ እገድላለሁ ማለቷ የሚታወስ ነው ። እናም የዚህ ተልእኮ አካል የሆኑ ሰላዮችን በቱርክ አሰማርታ ነበር ። እነዚህ የእስራኤልን ተልእኮ ያነገቡና የሀማስ አመራሮች ያሉበትን አነፍንፈው ተልእኳቸውን ለመፈፀም የተዘጋጁ 34 የሞሳድ ስላዮች በቱርክ ደህንነት መስሪያቤት በተደረገባቸው ክትትል በቁጥጥር ስር ውለው ዘብጥያ ተወርውረዋል ። ቱርክም ከእነዚህ ሰላዮች ላይ ተገቢውን መረጃ ሰብስባ ለቀጣይ ውሳኔዋ ትደርሳለች ተብሎ ይጠበቃል ። ቱርክ የሀማስ ጠንካራ የፖለቲካ ድጋፍ ሰጪ ሀገር መሆኗ የሚታወስ ነው ።

👉 ሀማስን ሙሉ በሙሉ ካላሸነፍን በመካከለኛው ምስራቅ ያለን ህልውና አደጋ ውስጥ ይወድቃል እንደ ሀገርም እንደ ህዝብም መቀጠል አንችልም ሲል የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር ዮአቭ ጋላንት ዛሬ ስጋቱን ገልጿል ። ጦርነቱ ከእስራኤል እቅድ ውጭ እየሄደ እንደሆነና ሀማስንም ማጥፋት የሚለው የእስራኤል ጎል እየከሸፈ መምጣቱ ለእስራኤል ህልውና አደገኛ ነገር አድርጎታል ። እናም መከላከያ ሚኒስትሩ ያለን አማራጭ ወይ ማሸነፍ ነው ወይ መጥፋት ነው ሲል ስጋቱን ገልጿል ። ፍልስጤማዊያንን " የሰው እንሰሳቶች" በማለት ጦርነቱን በእብሪት አስጀምሮ የነበረው ሚኒስትሩ ዛሬ ያ ትእቢቱና ጉራው ተንፍሶ ጭንቀት ውስጥ ገብቷል ።

ምንጭ

👉 t.me/Seidsocial

Mesaj olarak gönder
Sayfamda paylaş
Grupta paylaş