Translation is not possible.

……መታጠብ አያምርህም?……ከቆሸሽክ ቡኋላ…ከድካምህ ቡኋላ……ሁሉም ነገራቶች ከተጠናቀቁ ቡኋላ…መፅዳት፣ መታጠብ አያምርህም?…ልክ ነው ሁሉም ሰው ይሄን ፅዳት ይፈልገዋል…ሰው ስራ ውሎ ሲለፋ የዋለበትን ልብስ፣ድካም፣ላቡን በመታጠብ ሊያስወግደው ይፈልጋል……ግን የጅስምህ፣የልብስህ፣ፅዳት እንደዚ የሚያሳስብህ ከሆነ፣ኖርማል እንቅልፍ እንድትተኛ የሚረዳህ ከሆነ……ትልቁን መቋሸሽ ……ትልቁን መታጠብ ለምን ረሳህ…የቱን?ነው ያልከኝ:ነገ ቀብርህ የተመቻቸ የሚያደርግልህ ነዋ……ሙሉ ቀን… አንዴ በምላስህ ሰዎችን ስታብጠለጥል የዋልክበትን……እጆችህ መጥፎ እንድትሰራ ያደረጉህን……እግሮችን ወደ ወንጀል የወሰዱህን……ወንጀል የተባሉትን እንድትመለከት ያደረጉህን አይኖችህን……እንዴት ከዚህ ሁላ መቆሸሽ ቡኋላ ማጠብ ማፅዳት አያምርህም……ምናልባት የቆሻሻው መጠን አልታየክ ይሆን?ልክ ነው ድሮምኮ ውስጣዊ ቆሻሻዎች ከጎዱ ቡኋላ ነው የሚያስታውቁት አሏህ ያዘነለት ሲቀር……እናም ወዳጄ ወደ አልጋህ ስትሄድ ከላይ የቆሸሸውን ብቻ ሳይሆን በወንጀል የተጨማለቀውን ማንነትህን ሳታፀዳ ጎንህን ለመኝታ አታሳርፈው……ማን ያውቃል የዛች ቀን ለሊት የዱኒያ ላይ የመጨረሻዋ ቆይታህ ልትሆንም ትችላለችኮ……እናማ ቆሽሻለው ፣አልፀዳም ፣የኔ ነገር አብቅቷል አትበል……አንተ ብቻ ከነ ቆሻሻህ ከነ ወንጀልህ ከነ ብዙ ጥፋቶችህ ወደ ጌታህ ተጎተት እመን ካንተ መጎተት በፈጠነ መልኩ ጌታህ ወደ አንተ ሲቀርብ ይታወቅሀል……የሰራከው ወንጀል ከተውበት እንዳያርቅህ……ተስፋ እንዳያስቆርጥህ……ከወንጀሉ የከበደው ይሄ ስለሆነ……እናም ወደ ጌታህ ሂድ…አብሽር ሁሉም የራሱ የሆነ መፅጃ አለው።#ወንጀልም #በተውበት ይፀዳል።

لَلَّهُ أَشَدُّ فَرَحًا بِتَوْبَةِ عَبْدِهِ حِينَ يَتُوبُ إِلَيْهِ،

Send as a message
Share on my page
Share in the group