#ቤቲንግ
ብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ጨምሮ ሌሎችም ተቋማት ነገ ከጥዋቱ 2:30 ላይ የስፖርት ውርርድ ፈቃድ ከተሰጣቸው ድርጅቶች ጋር ሊመክሩ ቀጠሮ መያዛቸው ተሰምቷል።
ብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር ከአዲስ አበባ ከተማ የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ጋር በመተባበር አዘጋጀሁት ባለው የምክክር መድረክ ላይ ፤ የስፖርት ውርርድ ፈቃድ የተሰጣቸው ድርጅቶች ጥዋት 2:30 ላይ ቀበና አካባቢ በሚገኘው ራስ አምባ ሆቴል የስብሰባ አዳራሽ እንዲገኙ ጥሪ አቅርቧል።
አስተዳደሩ ነገ የድርጅት ሥራ አስኪያጅ ወይም አንድ ተወካይ እንዲገኝ ጥብቅ ማሳሰቢያ የሰጠ ሲሆን በውይይቱ ላይ የሚቀርቡ መረጃዎች፦
1. የድርጅቱ ቅርንጫፍ መ/ቤቱች ዝርዝርና ሙሉ አድራሻ / አዲስ አበባ እና ከአዲስ አበባ ውጪ ክልል ከተሞች የሚገኙ ቅርንጫፎች በተናጠል / ከተቻለም በቅርቡ በተደረገው ዘመቻ የተዘጉ ቅርንጫፎች እንዲለዩ ወይም የተለየ ምልክት እንዲደረግባቸው፤
2. የድርጅቱ ሠራተኞች ብዛት
3. የድርጅቱ የቴክኖሎጂ አቅራቢ ድርጅት ሥምና አገር ናቸው ብሏል።
በውይይቱ ላይ፣ የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ ቢሮን ጨምሮ የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ኮሚሽን፣ የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር፣ የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ እና የአዲስ ከተማ ገቢዎች ቢሮ ተወካዮች ይገኛሉ ተብሏል።
በቅርቡ በአዲስ አበባ ከተማ 3,241 የስፖርት ውርርድ (ቤቲንግ) ቤቶች ላይ የማሸግ እርምጃ መወሰዱ ይታወሳል።
የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ " ቤቲንግ " ቤቶቹን ለማሸግ ምክንያት ናቸው ያላቸው ፦
- ከስፖርት መጫወቻነቱ ባለፈ ሀገር ተረካቢ ትውልድን እያጠፋ በመሆኑ፤
- ከፍተኛ የወንጀል ማስፍፊያ እየሆነ በመምጣቱ፤
- የከተማውን ወጣት ግዜውን አላግባብ በስፍራው እያሳለፈ በመምጣቱ፤
- ከተፈቀደላቸው ፈቃድ ዉጪ እየሰሩ በመምጣታቸው፤
- የሰዉ ልጅ ህይወት አላግባብ እየጠፋ በመምጣቱ፤
- ተማሪዎችም ትምህርታቸውን ትተዉ በቦታው እየተገኙ በተገቢው መንገድም እንዳይማሩ በማድረጉ ፤
- የመማር ማስተማሩን ሂደት እያወከ በመምጣቱ የሚሉት እንደሚገኙበት አይዘነጋም።
ብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ጨምሮ ሌሎችም ተቋማት ነገ ከጥዋቱ 2:30 ላይ የስፖርት ውርርድ ፈቃድ ከተሰጣቸው ድርጅቶች ጋር ሊመክሩ ቀጠሮ መያዛቸው ተሰምቷል።
ብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር ከአዲስ አበባ ከተማ የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ጋር በመተባበር አዘጋጀሁት ባለው የምክክር መድረክ ላይ ፤ የስፖርት ውርርድ ፈቃድ የተሰጣቸው ድርጅቶች ጥዋት 2:30 ላይ ቀበና አካባቢ በሚገኘው ራስ አምባ ሆቴል የስብሰባ አዳራሽ እንዲገኙ ጥሪ አቅርቧል።
አስተዳደሩ ነገ የድርጅት ሥራ አስኪያጅ ወይም አንድ ተወካይ እንዲገኝ ጥብቅ ማሳሰቢያ የሰጠ ሲሆን በውይይቱ ላይ የሚቀርቡ መረጃዎች፦
1. የድርጅቱ ቅርንጫፍ መ/ቤቱች ዝርዝርና ሙሉ አድራሻ / አዲስ አበባ እና ከአዲስ አበባ ውጪ ክልል ከተሞች የሚገኙ ቅርንጫፎች በተናጠል / ከተቻለም በቅርቡ በተደረገው ዘመቻ የተዘጉ ቅርንጫፎች እንዲለዩ ወይም የተለየ ምልክት እንዲደረግባቸው፤
2. የድርጅቱ ሠራተኞች ብዛት
3. የድርጅቱ የቴክኖሎጂ አቅራቢ ድርጅት ሥምና አገር ናቸው ብሏል።
በውይይቱ ላይ፣ የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ ቢሮን ጨምሮ የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ኮሚሽን፣ የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር፣ የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ እና የአዲስ ከተማ ገቢዎች ቢሮ ተወካዮች ይገኛሉ ተብሏል።
በቅርቡ በአዲስ አበባ ከተማ 3,241 የስፖርት ውርርድ (ቤቲንግ) ቤቶች ላይ የማሸግ እርምጃ መወሰዱ ይታወሳል።
የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ " ቤቲንግ " ቤቶቹን ለማሸግ ምክንያት ናቸው ያላቸው ፦
- ከስፖርት መጫወቻነቱ ባለፈ ሀገር ተረካቢ ትውልድን እያጠፋ በመሆኑ፤
- ከፍተኛ የወንጀል ማስፍፊያ እየሆነ በመምጣቱ፤
- የከተማውን ወጣት ግዜውን አላግባብ በስፍራው እያሳለፈ በመምጣቱ፤
- ከተፈቀደላቸው ፈቃድ ዉጪ እየሰሩ በመምጣታቸው፤
- የሰዉ ልጅ ህይወት አላግባብ እየጠፋ በመምጣቱ፤
- ተማሪዎችም ትምህርታቸውን ትተዉ በቦታው እየተገኙ በተገቢው መንገድም እንዳይማሩ በማድረጉ ፤
- የመማር ማስተማሩን ሂደት እያወከ በመምጣቱ የሚሉት እንደሚገኙበት አይዘነጋም።