Çĕнĕ çулахне йывăçлăх

መልዕክተኛው ከባልደረቦቻቸው መሀል ቁጭ ብለው ህግጋቶችን እያስተማሯቸው ነው።ባልደረቦቹም ከመሀከላቸው የተቀመጡትን ነቢይ በስስት እየተመለከቱ እያዳመጡ ነው።

ድንገት አንድ የአይሁድ ሊቅ ሲንደረደር ወደ ስብስቡ መሀል ገብቶ ትሁቱን መልዕክተኛ አነቃቸው። ኮሌታቸው ጨፍግጎ ከያዘም በኋላ፦‹‹ብድሬን መልስ! ድሮም በኑ ሀሺም ጎሳዎች ብድር ታዘገያላችሁ›› እያለ ያንገላታቸው ጀመር።

ይህ ሰው በርግጥ ለመልዕክተኛው ገንዘብ ያበደረ ቢሆንም የተዋዋሉበት የመክፈያ ግዜ ግን አልደረሰም ነበር።

ቀና ብሎ ለማየት የሚሳሳላቸው ዑመር ረዐ ይህንን እንግልት ሲመለከት ብድግ ብሎ ሰይፉን ከማንገቻው መዘዘ'ና፦‹‹እባክዎ አንቱ ነቢ ይፍቀዱልኝና ይህን ሰው አንገቱን ልቀንጥስ›› አላቸው።

አንገታቸው የታነቀው ነቢይ ወደ ዑመር ዙረው ፍፁም በተረጋጋ አንደበት፦‹‹ተው እንጂ ዑመር! እኔ ብድሬን እንድመልስ ምከረኝ፣ እሱም በስርዐት እንዲጠይቀኝ አድርግ እንጂ ሰይፍን ምን አመጣው?›› አሉት።

የአይሁዱ ሊቅ ተረጋግቶ ቆመ። እንዲህም አለ፦‹‹በዕውነት በላከህ ጌታ እምላለሁ፤ ብድር ልጠይቅህ ሳይሆን የመጣሁት ትዕግስትህን ልፈትን ነው። በርግጥ ብድር መመለሻ ግዜህ አልደረሰም ነበር። ግና መገለጫዎችህን ሁሉ እኛ ዘንድ ባለው የኦሪት መፅሀፍ ስለተመለከትኩ አንድ ባህሪህን ብቻ ለማረጋገጥ ነው ዛሬ የመጣሁት።

ኦሪት ላይ እንዲህ ይላል" ያ ነብይ በቁጣ ግዜ ታጋሽ ነው፣ የመሀይማንም ጉንተላ ትሁትነትን እንጂ ሌላን አይጨምርለትም" አንቱ ነቢይ ሆይ! ዛሬ ይህን አረጋገጥኩ። ከአላህ ሌላ ጌታ እንደ ሌለ እመሰክራለሁ፤ አንቱም የአላህ ነቢይ መሆንዎን እመሰክራለሁ።

አንቱ ነቢ! ያ ያበደርኮት ገንዘብ ለድኾች ምፅዋት እንዲሆን ለግሻለሁ›› ብሎ እስልምናን ተቀበለ።

Хыпар пек ярас
Ман тетелӗ питра пайлас
Ушкӑнта пайлас