Translation is not possible.

አስቸኳይ መረጃ‼

=============

(ለሁሉም ይሰራጭ!)

||

✍ «ፕሮፌሰር ኢያሱ ኢሊያስ በተባለ የፓርላማ አባል አስተባባሪነት ህጋዊ የመስጂድ ካርታ እና የግንባታ ፍቃድ ያለው የመስጂድ ቦታ ግንባታ እንዳይደረግ ያለምንም ህጋዊ ምክንያት ታገደ ።

በኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ ወረዳ 5 አግራዉ  በሚል ስያሜ የሚታወቀው መስጂድ በትላንትናው እለት ግዚያዊ የመስጂድ  አጥር ግንባታ ለማድረግ እንቅስቃሴ በሚደረግበት ወቅት የወረዳው አመራሮች ከከንቲብ ጽ/ቤት ተደውሎልናል በሚል  ግንባታው እንዲቆም አድርገዋል ።

ያለ ህግ አግባብ እንዲታገድ ስለተደረገበት ሁኔታ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤት መረጃ ሲጠይቁ የአከባቢው ማህበረሰብ ቦታው ላይ መስጂድ እንዳይገነባ ፒትሽን ፈርሞ ስላስገባ ነው ካርታውን አምክነን ሌላ ተለዋጭ ቦታ እንሰጣቹሃለን የሚል ምላሽ ተሰጥቷል ።

ፕሮፌሰር እያሱ የተባለው የፓርላማ አባል መኖሪያ ቤቱ  ከመስጂዱ አጠገብ ሲሆን « እኔ እዚህ እያለው  በፍፁም አጠገቤ መስጂድ አይሰራም ‼ » በሚል በተለያየ ግዜ በአከባቢው ሙስሊሞች ላይ እንደሚዝትና በአከባቢው ላይ የሚገኙ ከ 90 የማይበልጡ የሌላ እምነት ተከታዮችን አስተባብረው ፒትሽን ማስገባቱን ለማወቅ ተችሏል  ።

ያለምንም የህግ አግባብ የመስጂዱ ግንባታ በመታገዱ ማህበረሰቡ በጊዚያዊነት የመስጂዱ ቅጥር ግቢ ውስጥ ድንኻን በመወጠር ሰላቱን በማከናወን ላይ ይገኛል።»

መላው ህዝበ ሙስሊም በነገው ዕለት ዘነበ ወርቅ አካባቢ 72 ባጃጅ ተራ አግራው ሰፈር በመገኘት የጁሙዓህ ሶላትን በህብረት በመስገድ መስጂዱን እንዲያስከብር ጥሪ ተላልፏል።

ሁሉም ሼር በማድረግ ላልሰማ ያሰማ።

መልዕክቱን ለሁሉም በማድረስ መስጅዳችንን እናስጠብቅ።

||

t.me/MuradTadesse

fb.com/MuradTadesseOfficial

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group