Translation is not possible.

የጀመርናቸው ጓደኝነቶች ሁሉ አይዘልቁም፤

መንገድ ያጃመሩን ሁሉ አብረዉን አይጨርሱም፤

እያንዳንዱ ሰው በሕይወታችን ዉስጥ የሆነ የሆነዉን ክፍል ወስዶ ይሄዳል፤

ከፊሉ ተራምዶ ይቆማል፤

ሌላው ሸኝቶ ይመለሳል ፤

ሌላው ረጅም ሄዶ ይጠፋል፤

ሁላችንም ምክንያቶች ምን ይሁን ምን የከሰሙና ያልተሳኩ ግንኙነቶች ይኖሩናል፣

ዐይብ ካለባቸው ተመልሰህ አትግለጥ፤

የሄዱ ሰዎችን ሚስጢር አታውራ፣

መልካም የነበሩ ጊዜያትን አስታውስና የግንኙነቶችን ክብር ጠብቅ፤

መመለስ የማትችለዉን ዘመን ወደኋላ አትጎትት፤

የተዘጋን መቃብር አትክፈት፤

ወረቀቱን ገልብጥና በአዲስ ገፅ ጀምር፤

ወደፊት ሂድ፤

ሕይወትህን ኑር፤

ባለህ ተደሰት፤

በተሰጠህ እርካ፤

በበለጡህ አትቅና፤

ለሰዎች ተደሰት፤

ለመደሰታቸዉም ምክንያት ሁን፣

እስከመጨረሻው አብሮህ የሚዘልቅ እሱ ነዉና

ቀልብህን በጥላቻና ቅናት አታጠልሸው፣

ሐቢቢ

ይህች ዱንያ እኮ በጣም አጭር ናት።

ለጥላቻ የሚበቃ ቦታ የላትም።

" ወሬ አታምጡልኝ፤ ሁላችሁንም እንደወደድኩ ልኑር ።" ይሉ ነበር ረሱላችን ሶ.ዐ.ወ።

እንደርሳቸው እንሁን።

ሶባሐል ኸይር

የምትወዱኝ ሼር አድርጉ።

https://t.me/MuhammedSeidAbx

Telegram: Contact @MuhammedSeidAbx

Telegram: Contact @MuhammedSeidAbx

ወደ ቤታችሁ እንኳን መጣችሁ
Send as a message
Share on my page
Share in the group