Translation is not possible.

የኛ ሃገር ባንኮች‼

=============

(ደሃን በጣም ደሃ አድራጊዎች፣ ባለ ሃብትን በጣም ባለ ሃብት አድራጊዎች!)

||

✍ ሚስኪኑ ወገኔ ሆይ! ዛሬ ባንኮች እንደት እንደሚቀፍሉህ ልጠቁምህ ወደድኩ።

ይህን የባንኮች አሠራር ምናልባት ከፊሎች ከናካቴው አያውቁትም፣ ከፊሎች አስተውለውት አያውቁም፣ ከፊሎች ቢያውቁትም አማራጭ ስለሌላቸው ውስጣቸው እየጨሰ ተላምደውት እየኖሩ ነው።

ባንኮች በየመንገዱ አስቁመውህ በ10 ብርም ቢሆን አካውንት ክፈት የሚሉህ ለአንተ አስበው ይመስልሃል? «ፎቶ አልያዝኩም!» ስትላቸው እንኳ «ችግር የለውም፣ ሌላ ጊዜ ታመጣለህ!» ይሉሃል። ሽል ለማለት ብለህ «አካውንት አለኝ!» ስትላቸው ሊያስምሉህ ይደርሳሉ።

✔ ባንኮች እንደት መሰለህ የሚሠሩት። ከአንተ በትንሹ 10 ብር ወሰዱ። እንዳንተ ያሉ 20 ሚሊዮን ሚስኪኖች አሉ። ስለዚህ ከእናንተ ስንት ሸቀሉ? 200 ሚሊዮን ብር! አስበው ከአንዳችሁ ኪስ የወጣው 10 ብር ስለሆነች ምንም ላትመስላችሁ ትችላለች።

ከፊሎቹ በየወሩ ከሚያገኟት ደመወዛቸው ላይ ቀንሰው ያገኟትን ያጠራቅማሉ። ባለ 10 ሺህ ብር ደመወዝተኛ ለቤት ኪራይ 5 ሺህ ብር፣ ለምግብና ተያያዥ ወጪዎች 3 ሺህ ብር አወጣና ቀሪዋን 2000 ብር ባንክ አስቀመጠ። ከ124+ ሚሊዮን ዜጎች መካከል እንደዚህ አይነት 10 ሚሊዮን ዜጎች ቢኖሩ፤ ከነዚህ ብቻ 20 ቢሊዮን ብር ይቀፈላል። አስበው! ከፊሎች በ10 ሺዎች፣ በመቶ ሺዎች፣ በሚሊዮን የሚያጠራቅሙ አሉ። የነርሱን ስንጨምረው አስበው።

የሚገርመው ይሄ ከሁላችንም የተሰባሰበ ገንዘብ የሚውልበት አላማ ነው።

ይሄ ከየሚስኪኑ የተጠራቀመ ገንዘብ ለባለሃብቶች በብድር መልክ ይሰጥና ቢዝነስ ይሠሩበታል። አንተ ሚስኪኑም ከአንተና መሰሎችህ በተሰባሰበው ከተከፈተወረ ቢዝነስ ከፍለህ ትጠቀማለህ። አስበው! በአንተው ብር ትርፍ ሲሠራብህ! አያምም?

*

√ የሚገርምህ አንተ መኪና ወይም ቤት ለመግዛት አስበህ በወቅቱ ያለው አንተ የምትፈልገው መኪና ዋጋ 1 ሚሊዮን ብር ቢሆንና የምትፈልገው ቤት ግምቱ 10 ሚሊዮን ብር ቢሆን፤ አንተ ለጊዜው ያለህ ለመኪና 800 ሺህ ብር ቢሆንና ለቤቱ 8 ሚሊዮን ብር ቢሆን፤ በቃ የአመት ገቢዬን አጠራቅሜ ቀጣይ አመት እገዛዋለሁ ስትል፤ አንተ እያጠራቀምከው ያለውን ገንዘብ ተጠቅመው እየነገዱበት ያሉት ከባንኩ ጀርባ ያሉ ባለሃብቶች ኑሮን አስወድደውት ያ ቀጣይ አመት ልታገኘው የተመኘኸው መኪና 1.5 ሚሊዮን ብር ሆኗል፣ ቤቱ 20 ሚሊዮን ብር ገብቷል። አሁንም ቀጣይ አመት ስትል በየጊዜው እየጨመረ እነርሱ ወደፊት እየሸሹህ፣ አንተ ከኋላ እየተከተልክ አባራሪና ተባራሪ ሆናችሁ እድሜህ ይገፋና አንድ ቀን ሞት ይመጣል።

ግን ራስህን እየጎዳህ ያለኸው አንተ ነህ። ኑሮን ለሚያስወድዱብህ ባለሃብቶች ከየትም ተሯሩጠህ ገንዘብ ፈልገህ በባንክ በኩል ታቀብላቸዋለህ።

አንዳንድ የግል ባንኮችማ አክሲዮን ብለው በጣት የሚቆጠሩ ሰዎች ይሰባሰቡና ከየቦታው አጠራቅመው ለራሳቸው ተከፋፍለው ይነግዱበታል። ይሄ ህዝብ ብዙ ያልገባው ነገር አለ።

እነዚያ ባለሃብት ተብዬዎች ግን ያላለቀ ህንፃቸውንና አሮጌ መኪናቸውን መያዣ አድርገው ያንተን ብር ተበድረው ይሠሩበታል። አንተ እንደነርሱ ተበድረህ እንዳትሠራ ቤትና መኪና የለህም። በቃ እንዲህ ሆነህ ውለታህ እንኳ ሳይቆጠር ማንንም ጠቃሚ ትሆናለህ።

*

√ ይሄ ይገርምሃል እንደ! ጭራሽ የወለድ ባንኮች ላይ ከወለድ አልባ በሚባለው መስኮት የሚያጠራቅም ሙስሊም አለ። እኔ'ምልህ ሐቢቢ! በዛ መስኮት የሰጡህ ብር ወለድ ካለበት መስኮት ላለመምጣቱ ምን ዋስትና አለህ? ሲጀመር እነርሱስ እንደት ብለው መቆጣጠር ይችላሉ?

ወይንስ የአንተ ከወለድ ነፃ ብሮች የተለዬ መልክ ስላላቸው እነዛን ለይተው ይስጡህ?

አትሞኝ! ንግድ ባንክ ከወለድ አልባ ያገኘውን ገቢ ዘምዘምና ሒጅራ ተደምረው አላገኙትም።

ቢያንስ ለሙስሊሞቹ ባንኮች ብትሰጣቸው ይበልጣል። ወንድሞችህ ይጠቀሙበት።

√ ምን ይሻል? ባንኮች አነስተኛ ገቢ ያለውንም ማኅበረሰብ ያማከለ ጥቅም እስኪዘረጉ ድረስ መታገል ግድ ነው። ሲጀመር የባለ ወለዶቹ እንደዛ ቢዘረጉም መጠቀም የለብንም። ከነርሱ ከናካቴው ውጡና ወደ ኢስላማዊ ባንኮች ዙሩ። ግን እነርሱም ጋ ገንዘባችሁን በአግባቡ ተጠቀሙበት።

እስኪ ሃሳብ አንሱና እንወያይበት። በተለይም መፍትሄው ላይ!

||

t.me/MuradTadesse

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group