Translation is not possible.

🕌ሀዲስ

የዛሬው ሀዲስ

.....................................

አቡ ሁሬይራ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት አንድ ሰው የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ዘንድ ቀረበና፡- ‹‹የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ሆይ! ይበልጥ ሎጎዳኘው የሚገባኝ ሰው ማንነው?›› አላቸው፡፡ ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) ‹‹እናትህ›› አሉት፤ በድጋሚ ‹‹ከዚያስ ቀጥሎ ማንነው?›› አላቸው፤ ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) ‹‹እናትህ›› አሉት፡፡ ሰውዬው ‹‹ከዚያስ ቀጥሎ?›› አላቸው፡፡ ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) ‹እናትህ›› አሉት፡፡ (ለአራተኛ ጊዜ) ‹‹ከዚያስ ቀጥሎ?›› አላቸው፡፡ ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) ‹‹አባትህ› አሉት፡፡

📚ሐዲሱን ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል

በሌላ ዘገባ ደግሞ ‹‹የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ይበልጥ ልጎዳኘው የሚገባኝ ሰው ማንነው?›› ብሎ ጠየቃቸው፡፡ ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ) ‹‹እናትህ ከዚያም እናትህን ከዚያም እናትህን ከዚያም የቅርብ ዘመድህን ከዚያም የቅርብ ዘመድህን›› አሉት፡፡

1️⃣ እናት ከልጁ መወለድ እስከ ሞቱ ድረስ ከፍተኛ መስዋዕትነት የከፈለችና የምትከፍልም በመሆኗ ከፍተኛ አትኩሮት ለመስጠት ነው፡፡

2️⃣ የእናት ደረጃ ከአባት የበለጠ ከፍተኛ ስፍራ እንዳለው ማሳያ ነው፡፡

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group