Translation is not possible.

እስራኤል በአለምአቀፉ የወንጀለኛ ፍርድ ቤት መከሰስ አለባት- የቱርኩ ኢርዶጋን

ህዳር 19/2016

የጋዛ የጤና ባለስሌጣናት ባወጡት መረጃ መሰረት እስራኤል በአየር እና በእግረኛ ጦር ባደረሰችው ጥቃት ከ15ሺ በላይ ፍልስጤማውያን ተገድለዋል

ኢርዶጋን እስራኤል በጋዛ ፈጽማዋለች ላሉት የጦር ወንጀል በአለምአቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት መከሰስ አለባት ሲሉ ለተመድ ኃላፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ተናገሩ።

የጋዛ የጤና ባለስሌጣናት ባወጡት መረጃ መሰረት እስራኤል በአየር እና በእግረኛ ጦር ባደረሰችው ጥቃት ከ15ሺ በላይ ፍልስጤማውያን ተገድለዋል።

እስራኤል ጥቃት የጀመረችው ሀማስ ባለፈው ጥቅምት ወር የእስራኤልን ድንበር በመጣስ በ50 አመታት ውስጥ ከባድ የተባለ ጥቃት ማድረሱን ተከትሎ ነው።

ከተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ጉባኤ አስቀድሞ ባደረጉት የስልክ ንግግር ኢርዶጋን እና ጉተሬዝ "ህጋዊ ባልሆነው የእስራኤል ጥቃት"፣ በሰብአዊ እርዳታ አቅርቦት እና በዘላቂ ተኩስ አቁም ዙሪያ ማውራታቸውን የቱርክ ፕሬዝደንት ጽ/ቤት አስታውቋል።

በንግግሩ ወቅት የቱርኩ ፕሬዝደንት እስራኤል አለምአቀፍ ህግን እና  አለምአቀፍ የሰብአዊ መብት ህግን ያለሀፍረት በመጣሷ ለሰራችው ወንጀል በአለምአቀፍ ህግ ፊት ተጠያቂ መደረግ አለባት ብለዋል።

የቱርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንደገለጸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሀካን ፊዳን በኒው ዮርክ በሚካሄደው የጸጥታው ምክር ቤት ስብሰባ ይሳተፋሉ።

ከስብሰባው ጎንለጎን ሚኒስትሩ ከአረብ ሀገራት ከሚመጡ አቻቸው ጋርም ይወያያሉ ተብሏል።

እስራኤል በጋዛ እያካሄደች ያለውን ዘመቻ በጽኑ የምትቃወመው ቱርክ ተኩስ አቁም እንዲደረግ እና በ'ቱ ስቴት ሶሉሽን' ላይ ውይይት እንዲደረግ ጥሪ አቅርባለች።

ኢርዶጋን እስራኤል በጋዛ እያደረገች ያለውን ጥቃት "ዘር ማጥፋት" ነው ማለታቸውም ይታወሳል።

ነገርግን እስራኤል የቱርክን ውንጀላ አትቀበለውም።

በእስራኤል እና ሀማስ መካከል የነበረው ጦርነት በኳታር አደራዳሪነት ጋብ በማለቱ ታጋቾች እና እስረኞች ተለቀዋል።

Join us

🇵🇸🇵🇸🇵🇸

https://t.me/Ihsan_media_1

https://ummalife.com/ihsan_midea

https://www.youtube.com/@ihsan_media1

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group