Translation is not possible.

ሀመር ተመልሼ ዳዕዋ መስጠት ጀመርኩ 15 ሰዎችን በአንድ ጊዜ ሳሰልም " በአጋንንት እየመረዛቸው ነው ተብዬ ታሰርኩ

ለሳምንት ቆይቼ ከእንግዲህ ዳዕዋ ላለመስጠት አስፈርመው ለቀቁኝ ዳዕዋዬን ግን አላቋረጥኩም ነበር ።

በሌላ ቀን 30 ወጣቶችን አስልሜ በሚስጥር ያዙት አልኳቸው ለምን? የምን መደበቅ ነው እንደውም ጣቢያ እንሂድ ብለው ተያይዘን ሄድን

ዳዕዋ ሰጥቶን እስልምናን ተቀብለን ነው አሉ ሁላችንንም አሰሩን በሳምንቱ ተፈታን እስሩን ለመድኩት ዳዕዋ እየሰጠሁ ካሰለምኩ በኃላ መስገጃዬን ይዤ ጣቢያ በመሄድ አስልሚያለሁ እሰሩኝ ማለት ጀመርኩ ለብዙ ጊዜ ሳሰልም ለሳምንት እየታሰርኩ ስለቀቅ በመጨረሻ ሰለቹኝ በቃ እንዳትመጣ እንደፈለግክ ብለው ለቀቁኝ

በነፃነት ዳዕዋ መስጠት ጀመርኩ.. እናቴ ፣ እህቶቼ ፣ ወንድሞቼን ጨምሮ ብዙ ሰዎች በእጄ እስልምናን ተቀበሉ አልሃምዱሊላህ

ዳግማይ ሀበሻዊው ቢላል

Send as a message
Share on my page
Share in the group