Translation is not possible.

#ህይወቱን_ለመስጅዱ

ግንቦት 18/09/2015 ዓ.ል ዕለተ ጁምዐ በሸገር ከተማ መልሶ ማልማት መስጂድ ፈረሳ በታላቁ አንዋር መስጂድ በተደረገው ተቃውሞ ላይ የፀጥታ ሀይሎች በወሰዱት ዕርምጃ ብዙ ወንድሞቻችን እንደሞቱና እንደተጎዱ ይታወቃል ከነዚህም ውስጥ አንዱ የሆነው ወንድማችን ሁሴን ሙህዲን በደረሰበት ከፍተኛ የሆነ ድብደባ በጭንቅላቱና በነርቩ ላይ ከባድ ጉዳት ደርሶበት እንደ ነበር እና ከአንድም ሁለት ጊዜ በጥቁር አንበሳና በአሚን ሆስፒታል የጭንቅላት ቀዶ ጥገና ተደርጎለት በመልካም ጤንነት ላይ የነበረ ሲሆን

አሁን ላይ ግን ከቀን ወደ ቀን የጤንነት ሁኔታው እየከፋ በመምጣቱ በአስቸኳይ ወደ ወጪ ሀገር ሄዶ ህክምና እንዲደረግለት በዶክተሮች ተወስኗል ለህክምናው ወጪ 2.9 ሚልዮን ብር ያስፈልገዋል ይህ ደግሞ ከቤተሰቦቹ አቅም በላይ ስለሆነ ከጎኑ እንድትቆሙልን ስንል በትህትና እንጠይቃለን ።

"የበጎ ስራ ምላሹ በጎ እንጂ ሌላ አይደለም "

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group