Translation is not possible.

ኢብኑ ሙፍሊሕ አልሐንበሊይ በዘመናቸው እንዲህ ብለው ነበር ፦

ከሰዎች ሁኔታ በጣም የተገረምኩበት ና የገመገምኩት ነገር፡ ሀገር በመውደሙ፤ የቅርብ ዘመዶችና ቀደምቶች  በመሞታቸው፤ በሪዝቅ(ሲሳይ) ማነስ ምክንያት መቆጨት፤ ያሉበትን ዘመን እና የዘመኑን ሰው መውቀስ፤ የህይወትን መክበድ እንዲሁም የኑሮ ውድነትን ና በሀገር መሪዎች በደል በተደጋጋሚ ሲጮሁ መመልከታችን ነው ።

ነገር ግን የኢስላምን ውድመት፤ የሰዎችን ከመስጊድ መራቅ፤የሱናን መሞትና የቢድዓን መሰራጨት፤ (የሰዎችን) የሸሪዓ ወንጀሎችን (እንደ ቀላል) መፈፀም  እየተመለከቱ ከነሱ ውስጥ ለዲኑ ሲል የጮሀ፤ የአላህን ሐቅ በማጓደሉ ያለቀሰ፤ ግዜው (ለአኼራው የሚሆን ምንም   ነገር ሳይሰራበት) በማለፉ የተቆጨ ሰው አላገኘውም ። ለዚህም ሁኔታቸው ምክኒያቱ ለዲነል-ኢስላም ያላቸው ቦታ መቅለሉ የዲኑ ጉዳይ ደንታ የማይሰጣቸው በመሆናቸው ና ዱንያ አይናቸው ላይ በመግዘፏ እንደሆነ ብቻ ነው የሚታየኝ ።

📚 الآداب الشرعية(240/3)

ያ አላህ ሼይኹ በሳቸው ዘመን ይህን ማለታቸውን ያስተዋለ የኛን ዘመን ቢያዩት ምን ይሉ ነበር የሚል ጥያቄ ማንሳቱ አይቀርም

            አሏሁመ ሰሊም ሰሊም

5 views
Send as a message
Share on my page
Share in the group