ترجمہ ممکن نہیں

ጥበበኛው ሉቅማን ረሒመሁላህ ልጃቸውን እንዲህ በማለት መከሩት፡-

‹ልጄ ሆይ! ባንተና በተስፋህ መካከል ግርዶ እስኪፈጠር ድረስ አላህን ለመፍራት ተጣጣር፡፡ ባንተና በአላህ ፍራቻ መካከል ግርዶ እስኪሆን ድረስ በአላህ ላይ ተስፋ አድርግ፡፡›

ልጅም ‹አባቴ ሆይ! እኔ ያለኝ ቀልብ አንድ ነው፡፡ በአላህ ፍራቻ ያጠመድኩት እንደሆነ ከአላህ እዝነት ተስፋ ይቆርጣል፡፡ በአላህ የእዝነት ስፋት ከጠመድኩት ደግሞ አላህን መፍራት ይተዋል፡፡› አላቸው፡፡ እርሳቸውም እንዲህ አሉት ‹አማኝ ሁለት ቀልብ እንዳለው ሆኖ ነው የሚኖረው፡፡ በአንደኛው በተከበረውና በላቀው አላህ ላይ ተስፋ ያደርጋል፤ በሌላኛው ደግሞ ይፈራዋል፡፡›

Send as a message
Share on my page
Share in the group