Tidak bisa diterjemahkan.

አዲስ የተጀመረ ብልሹ ዐቂዳህና መንሃጅ መጥቷል አሉ። መጥተው የነበሩት እነ አሕባሽ ወደመጡበት ሳይመለሱ ሌላ ደግሞ እየተሳበልን ነው።

ይህ አዲሱ ዐቂዳ እነ ዶ/ር ጀይላንና ሌሎችም ታዋቂ ኡስታዞች በሚገኙበት አየር ጤና አንሷር መስጂድ መሰበኩ ደግሞ አሳሳቢ ነው። በርግጥ ዶ/ር ጀይላን ከደርሱ በኋላ ረድ ሰጥተዋል የሚል መረጃ ሰምቻለሁ።

የሚያሳዝነው አንዳንድ የአየር ጤና ወንድሞች አዲሱን አካሄድ «ትክክል ነው!» ብለው ለመከራከር እየሞከሩ ነው አሉ።

ለማንኛውም ስለዚህ መንገድ ቀደም ብሎ ሰበካው ያገኘው ኡስታዝ አቡበከር ሑሴን በቪድ የሚያውቀውን ያክል በሚገባ አብራርቷልና የመጀመሪያ ደረጃ መረጃ ስላለው ከራሱ አንደበት አዳምጡት።

በመስጅድ፣ መድረሳና ኢስላማዊ ማዕከል ግንባታ ሽፋን የሚመጡ አዳዲስ አካሄዶች (በተለይም ይህ አብርሃማዊ ኃይማኖቶች) የሚለው እሳቤ ተያይዘው እንዳይመጡ መጠንቀቅ ያሻል የምንለው ለዚህ ነው።

ለገንዘብ ተብሎ ትክክለኛ ዐቂዳህ አይሸጥም። ከትክክለኛ ዐቂዳችን ጋር ድህነታችን ይበልጥብናል

ይህ አዲሱ ዐቂዳህ ግን የምን አራቱ አኢማዎች፣ የምን መዝሃብ፣ የምን ሰለፎች… ሁሉንም የሚያንኮታኩት አደገኛ አካሄድ ስለሆነ ሳይስፋፋ በአስቸኳይ ከሃገር መውጣት አለበት።

ከዘገየ ግን እያንዳንዱ የጥመት ተጣሪ ተከታይ አያጣም። እንኳን እነዚህ አስመሳዮቹ በፍቅርሲዚም የሚያምን ከንቱ መች ይጠፋል!

||

t.me/MuradTadesse

Kirim sebagai pesan
Bagikan di halaman saya
Bagikan di grup