Terjemahan tidak mungkin.

እንግሊዝ በተቃውሞ እየተናጠች ነው !

የእንግሊዝ ፓርላማ የአስቸኳይ ጊዜ ስብሰባ ጠርቷል !

በእንግሊዝ የሚደረገው የፍልስጤማውያን የድጋፍ ሰልፍ የእንግሊዝ መንግስትን ወንበር እየነቀነቀ ነው። ትውልደ ህንዳዊው ሪሺ ሱናክ የሚመራው የእንግሊዝ መንግስት ለእስራኤል የማያወላውል ድጋፍ ሲሰጥ መቆየቱ ይታወቃል። ጠቅላይ ሚኒስትር ሪሺ ሱናክም እስራኤል ድረስ በመሄድ "ብቻሽን አይደለሽም እንግሊዝ ከጎንሽ አለች" ብሎ የመሰረተቻት ሀገር አሁንም እንደማትተዋት ገልፆ ወደ እንግሊዝ ሲመለስ ግን የገጠመው የእንግሊዝ ህዝብ ቁጣን ነው።

ለንደን የፍልስጤም ከተማ እየመሰለች ነው። እናም ነገ እጅግ ከባድ የሆነ የፍልስጤማውያን የድጋፍ ስልፍ በመጠራቱ መንግስት ከፍተኛ ስጋት ውስጥ ወድቋል።

በመሆኑም የእንግሊዝ መንግስት ማምሻውን ባወጣው መግለጫ አስቸኳይ የፓርላማ ስብሰባ የጠራ ሲሆን በፍልስጤም እና በእስራኤል ላይ ያለውን አቋም እንደሚያሳውቅም ገልጿል። እናም መንግስት ለእንግሊዝ ህዝብ ባስተላለፈው ጥሪ የነገን ብቻ እንዲጠብቁ እስከ ውሳኔው ድረስ በትእግስት እንዲጠብቁ ተማፅኗል።

እንግሊዝ እየተነሳባት ባለው የህዝብ ቁጣ ከአቋማ እየተንሸራተተች ሲሆን የተመድ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ድምፀ ተአቅቦ ማድረጓ ይታወቃል።

ፍልስጤሞች የምእራቡን አለም ህዝብ እያሸነፉ ሙምጣታቸውና ምእራባውያን ህዝቦች ለእስራኤሎች ያላቸው ጥላቻ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱ እስራኤልን እና አሜሪካን በከፍተኛ ሁኔታ ስጋት ውስጥ ከቷቸዋል።

መረጃው ሌሎች ጋር እንድደርስ ሸር ማድረጋችሁን አትርሱ።

image
Hantar sebagai mesej
Kongsi di halaman saya
Kongsi dalam kumpulan