Translation is not possible.

አሏህ ከዐርሽ በላይ ለመሆኑ ከሐዲስ ብቻ ማስረጃ

=~~~~~~~~=

የአላህ መልእክተኛ አላህ ከሰማያት ከዐርሽ በላይ መሆኑን በማያሻማ መልኩ ገልፀዋል፤ አላህ ከዐርሽ በላይ መሆኑን ከሚያረጋግጡ የሀዲስ ማስረጃዎች በጥቂቱ እንመልከት፡

قَال النَّبِيَّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: «أَلاَ تَأْمَنُونِي وَأَنَا أَمِينُ مَنْ فِي السَّمَاءِ›› صحيح البخاري4351

ነብዩ صلى الله عليه وسلم እንዲህ ብለዋል፡

‹‹ በሰማይ ያለው(አላህ) አምኖኝ ሳለ አታምኑኝምን››ቡኻሪ 4351

ሙዓውያ ኢብኑ ሀከም ፍየሎችን የምትጠብቅለት አገልጋይ ነበረችው እና ተኩላ በላባት ተበሳጭቶ መታት፤ ይህም ለነብዩ صلى الله عليه وسلم ነገራቸው በዚህም ነብዩ صلى الله عليه وسلم አከበዱበት…

قُلْتُ: يَا رَسُولَ اللهِ أَفَلَا أُعْتِقُهَا؟ قَالَ: «ائْتِنِي بِهَا» فَأَتَيْتُهُ بِهَا، فَقَالَ لَهَا: «أَيْنَ اللهُ؟» قَالَتْ: فِي السَّمَاءِ، قَالَ: «مَنْ أَنَا؟» قَالَتْ: أَنْتَ رَسُولُ اللهِ، قَالَ: «أَعْتِقْهَا، فَإِنَّهَا مُؤْمِنَةٌ» مسلم 1/381

‹‹የአላህ መልእክተኛ ሆይ ነፃ ላውጣትን›› አልኳቸው እሳቸውም‹‹ ወደኔ አምጣት አሉኝ›› ወደ እሳቸው አመጠኋት እና እንዲህ አሏት ‹‹አላህ የት ነው›› እሷም ‹‹በስማይ›› አለች እሳቸዉም ‹‹እኔ ማነኝ አሏት›› እሷም ‹‹ አንቱ የአላህ መልእክተኛ ናቹህ›› አሳቸው እንዲህ አሉ‹‹ ነፃ አውጣት እሷ ሙእሚን ነች››ሙስሊም ዘግበዉታል 1/381

–_

ከሀዲሱ እንደምንረዳው የአላህ መልእክተኛ እምነቷን ካረጋገጡበት አንዱ አላህ ከሰማያት በላይ መሆኑን መመስከሯ ነው፤በዚህ ዘመን አላህ የት ነው አይባልም በሚል ለሚሞግት ሰው በቂ ማስተማሪያ ነው! ልብ ካላቸው!!

አላህ በስማይ ነው ስንል በሰማይ ዉስጥ ሳይሆን ከሰማያት በላይ መሆኑን እና ‹ፊ› የሚትለዋ ፊደል በላይ የሚል ትርጉም እንዳላት ከላይ ስለተመለከትን የሚያወዛግበን አይመስለኝም፡፡

قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: «لَمَّا قَضَى اللَّهُ الخَلْقَ كَتَبَ فِي كِتَابِهِ فَهُوَ عِنْدَهُ فَوْقَ العَرْشِ إِنَّ رَحْمَتِي غَلَبَتْ غَضَبِي»صحيح البخاري 3194

የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል፡

‹‹ አላህ ፍጥረታትን(ፈጥሮ) እንደጨረሰ እሱ ዘንድ ከዓርሽ በላይ ካለው መፅሓፉ እዝነቴ ቁጣዬን ቀድማለች ብሎ ፃፈ፡፡›› ሶሂህ አል-ቡኻሪ 3194

ከዚህ ሀዲስ በማያሻማ መልኩ የምንረዳው አላህ ከዐርሽ በላይ መሆኑን ነው፡፡

عَنْ أَنَسٍ قَالَ: فَكَانَتْ زَيْنَبُ تَفْخَرُ عَلَى أَزْوَاجِ النَّبِيِّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ تَقُولُ: زَوَّجَكُنَّ أَهَالِيكُنَّ، وَزَوَّجَنِي اللَّهُ تَعَالَى مِنْ فَوْقِ سَبْعِ سَمَوَاتٍ.‹‹صحيح البخاري 7420

አነስ (ረድየሏሁ አንሁ) እንዳስተላለፉት፡ ዘይነብ በነብዩ ሚስቶች ላይ ስትፈክር ነበር እንዲህም ትላለች‹‹ እናንተን የዳሯቹህ ቤተሰቦቻቹህ ናቸው እኔን ግን ከሰባት ሰማያት በላይ(ያለው) አላህ ነው የዳረኝ፡፡›› ሶሂህ አል-ቡኻሪ 7420 በሌላ የቲርሚዚ ዘገባ ደግሞ፡

لَمَّا نَزَلَتْ هَذِهِ الْآيَةُ فِي زَيْنَبَ بِنْتِ جَحْشٍ {فَلَمَّا قَضَى زَيْدٌ مِنْهَا وَطَرًا زَوَّجْنَاكَهَا} [الأحزاب: 37]

አነስ(ረድየሏሁ አንሁ) እንዲህ ብለዋል ‹‹ ዘይድም ከእርሷ ጉዳይን በፈጸመ ጊዜ እርሷን አጋባንህ፡፡›› ይህ የቁርአን አንቀፅ በዘይነብ ቢንት ጀሕሽ በወረደ ግዜ ዘይነብ በነብዩ ሚስቶች ላይ ስትፈክር ነበር እንዲህም ትላለች‹‹ እናንተን የዳሯቹህ ቤተሰቦቻቹህ ናቸው እኔን ግን ከሰባት ሰማያት በላይ(ያለው) አላህ ነው የዳረኝ፡፡›› ቲርሚዚ 3213

عَنْ أَبِي حَازِمٍ، عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: «وَالَّذِي نَفْسِي بِيَدِهِ، مَا مِنْ رَجُلٍ يَدْعُو امْرَأَتَهُ إِلَى فِرَاشِهَا، فَتَأْبَى عَلَيْهِ، إِلَّا كَانَ الَّذِي فِي السَّمَاءِ سَاخِطًا عَلَيْهَا حَتَّى يَرْضَى عَنْهَا» مسلم 1436

አቡ ሁረይራ(ረድየሏሁ አንሁ) እንደዘገቡት የአላህ መልክተኛ እንዲህ ብለዋል፡ ‹‹ ነብሴ በእጁ በሆነው እምላለው አንድ ወንድ ሚስቱን ለምኝታ ጋብዟት እምቢ አትለውም ፤ ያበሰማይ ያለው በሷ ላይ የተቆጣባት ቢሆን እንጂ እሱ(ባሏ) ከእርሷ እስኪወድ ድረስ፡፡››

عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عَمْرٍو قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: «الرَّاحِمُونَ يَرْحَمُهُمُ الرَّحْمَنُ، ارْحَمُوا مَنْ فِي الأَرْضِ يَرْحَمْكُمْ مَنْ فِي السَّمَاءِ، …»:الترمذي 1924 حَدِيثٌ حَسَنٌ صَحِيحٌ

አብደላህ ኢብኑ ኡመር(ረድየሏሁ አንሁማ) እንደዘገቡት የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል፡

‹‹ አዛኞችን አር-ራህማን(አዛኙ አላህ) ያዝንላቸዋል፤ በመሬት ላሉት እዘኑ በሰማይ ያለው(አላህ) ያዝንላችኋል››ቲርሚ ዘግበዉታል 1924 ሀዲሱ ሶሂህ ነው

ብዙ ሀዲሶችን መጥቀስ ቢቻልም ፅሁፉ እንዳይረዝም ከላይ የጠቀስናቸው ሶሂህ ሀዲሶች አላህ ከሰማያት በላይ ከዓርሽ በላይ መሆኑን ያረጋግጣሉ፤ አላህ ያጠመመው ቢሆን እንጂ ይህንንም የሚያስተባብል የለም፡፡

Send as a message
Share on my page
Share in the group