Translation is not possible.

አሏህ የሙሽሪኮች ተግባር አንድ በአንድ ከንቱና ውድቅ መሆኑን አብራርቶ ሲያበቃ ሽርክ ለባለቤቱም የሚያስከትለው አደጋም እንደዚሁ አብራርቷል፦

(አላህ በእርሱ ማጋራትን በፍጹም አይምርም፡፡ ከዚህ ሌላ ያለውንም (ኀጢአት) ለሚሻው ሰው ይምራል፡፡ በአላህም የሚያጋራ ሰው ታላቅን ኀጢአት በእርግጥ ቀጠፈ፡፡) አኒሳዕ ፡48

(ይህ የአላህ መምሪያ ነው፡፡ በእርሱ ከባሮቹ የሚሻውን ሰው ይመራል፡፡ ባጋሩም ኖሮ ይሠሩት የነበሩት ከነሱ በታበሰ ነበር፡፡)አልአናም፡88

ነብዩ በሀዲሳቸውም" ከአሏህ ውጭ ሌላን ሲጣራ የሞተሰው እሱ የእሳት ነው" እንዳሉት በአሏህ ማጋራትን በተመለከተ የመጡ የቁራዓንና የሀዲስ መረጃዎች በጣም በርካታ ከመሆናቸው የተነሳ በዚህ ፅሁፍ ማካተት ከባድ ቢሆንም በጥቅሉ ሽርክ በሰው ልጅ ላይ ከሚያስከትለው ጉዳት መካካል ከአሏህ ውጭ ጉዳትም ይሁን ምንም አይነት ጥቅም የማያመጡለትን ለራሳቸው የአሏህ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው አካላትን ወይም የመያውቁትንና የማይሰሙትን አካላት በመተናነሱ ምክንያት የሰውን ልጅ ክብር ያሳጣል፣ ሰዎች ከመልካም ስራ ያዘናጋል፣ ሰዎች በመጥፎ ስራ እንዲዘወትሩ ያደርጋል፣ለሰው ልጅ የስጋትና የፍርዓት ምንጭ ይሆናል፣

የህዝቦች መለያየት ሰበብ ይሆናል፣ሰዎች በጀኸነም ውስጥ ዘውታሪ እንዲሆኑ ምክንያት ይሆናል።

አህባሾች ቁራዓንና ሀዲስ በቅጡ ባለመረዳት የሽርክ ምንነትና አደገኝነት ባለማወቅ የዲነል ኢስላም መሰረታዊ የሆነውን ተውሂድ ወደዃላ በማድረግ ተራውን አላዋቂ ማህበረሰብ ቀድሞ ባለማወቅ የሚፈፅማቸው መሰረተ ቢስ ነገሮች በአዲስ እምነት አድርገው በመያዝና እንዲመለሱበት በማድረግ የተለያዩ ከአሏህ ውጭ የሚመለክባቸው ቦታዎች አመታዊ መሰብሰቢያዎች፣ወለይዎች ብለው በሚሞግቷቸው ግለሰቦች መቃብር በመገኘት እንደዚሁም ማህበረሰቡን በመቀስቀስና ዳዕዋ በማድረግ ገንዘብ በመሰብስና በማስተባበር በነብዩ መውሊድና በወልዩቻቸው መውሊድ የተለያዩ ከእስልምና የሚስወጡ ተግባራትና ሁራፋቶች ከአሏህ ውጭ ባሉአካላት በሞተም ይሁን እሩቅ በሆነ አካል እርዳታን ይጠይቃሉ ድረስልኝ፣ ጠብቀኝ፣ነብዩን እጄን ያዙኝ፣ወንጀሌን ማረኝ ሲሉና ሲለምኑእና ሌሎች የሽርክ ተግባራትን ሲፈቅዱና እነርሱም ሲሰሩና ይስተዋላል።

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group