Translation is not possible.

ፎቶ ①: ወራሪዋ እስራኤል በጋዛ ከተማ ንጹሐን ነዋሪዎች ላይ ህፃናት፣ ሴቶችና አረጋውያን፣ ት/ቤትና ሆስፒታል፣ መጠለያ ካምፕና የእምነት ተቋም ሳትለይ እየፈጸመችው ያለ ያላባራ የቦምብ ማዕበል

ፎቶ ②: ባለፉት 24 ሰዓታት ብቻ ወራሪዋ የምድር ጦር ጋዛ ላይ ስለጀመረች የተገደሉባት 11 ወታደሮች

√ አሸባሪዋ አሜሪካ በምትሰጣት ዘመናዊ የጦር መሳሪያ በአየር ቦምብ በማዝነብ እንጂ እንደ ጀግና ፊት ለፊት ገጥሞ በማሸነፍ'ማ የለችበትም። ልብ ከየት ተገኝቶ!

ጦርነቱ ከተጀመረ 26ኛውን ቀን ይዟል። ወራሪዋ በተለመደው የአሜሪካና አጋሮቿ እገዛ በ1967 በ6 ቀን አሸንፊያለሁ ብላ ስትጎረር ነበር። ግን የአንድት መንደር ታጣቂ ሐማስ የተባለ ቡድን ብቻውን ይሄው አንድ ወር ገደማ ቀጥ አድርጎ ይዟታል። ያውም እርሱ ከአላህ ውጭ ማንም ደጋፊ የለውም። እርሷ ግን የዓለማችን ቁጥር አንድ ጦረኛ በሆነችው አሜሪካና ኃያላን በሚባሉት የአውሮፓ ሃገራት ያላሰለሰ ድጋፍ እየተደረገላት ነው። ጉራ ብቻ መሆኗን ዓለም ታዝቧል። እነዚህ አጋሮቿ ባይኖሩ ኖሮ ደግሞ በ26 ሰዓታት ውስጥ ብቻ ሐማስ እስራኤልን ተቆጣጥሮ ሊያስገብራት ይችላል።

ከዚህ በተጨማሪ ከዐረብ ሃገራት በባሰ መልኩ ሌሎች ሰብዓዊነት ከተሰማቸው ሃገራት ከፍተኛ ዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲያዊ ክስረት አጋጥሟታል። እንደ ኮሎምቢያ፣ ቺሊና ቦይሊቪያ ያሉ ሃገራት አምባሳደሯን ከማባረር ጀምሮ ከርሷ ጋር ያላቸውን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እስከማቋረጥ ደርሰዋል። ከባለፈው የተመድ ጠቅላላ ጉባዔ ጀምሮ በርካታ የአውሮፓ ሃገራትም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየከዷት መሆኑን የሚያሳይ አቋም አንጸባርቀዋል። ኢንሻ አላህ ቀስ በቀስ ከዓለም የተነጠለች ብቸኛ ተገፊ መሆኗ አይቀርም።

ጋዛዊያን ግን እንኳን የጦር መሳሪያ ምግብና ውሃ እንኳ እንዳያገኙ ተደርገው ይሄው በፅናት እያሳለፉ ነው።

አላህ ነስሩን ያቅርብላቸውና!

image
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group