Translation is not possible.

━┈የጥበብ ጫፍ ┅━

አንድ የሁዳዊ ወደ ሩቅ ሀገር እይተጓዘ ሳለ በመሀል የሙስሊሞች ሀገር ይደርሳል።

ያው እንደምታውቁት ይሁዳ ሁሌም ሸር እንዳሰበ ነው።

እናም፦"እዚህ ከተማ ገብቼ ዑለማኦችን ማደናገር አለብኝ" ብሎ ያስባል።

ከዚያም ከተማዋን ሊገባ ሲል አንድ እረኛ ያጋጥመውና በሱ ሊጀምር ወሰነ እና እንዲህ በማለት ጨወታ ጀመረ፦"እኛ ሙስሊሞች እኮ ቁርአን ለመሀፈዝ በጣም እየተቸገርን ነው።

አንደኛ፦30 ጁዝ ነው በዝቷል።

ሁለተኛ፦አንቀፆችም በጣም ብዙ ናቸው።

ሶስተኛው እና አስቸጋሪው ፦ ቁርአን ውስጥ ድግምግሞሽ አለ።

ስለዚህ ለምን የተደጋገሙ አንቀፆችን አንሰርዝም? ምክንያቱም የቃላት መደጋገም ነው እንጂ ምንም አይደለም።

ድግምግሞሹን ከሰረዝን መሀፈዙም ይቀለናል።"

የሁዳው ይሄን ሁሉ ሲያወራ እረኛው በፅሞና ያዳምጠው ነበር።

ከዚያም እረኛው ቀና አለና፦"ንግግርህ በጣም ደስ ይላል አሪፍ ሀሳብ ነው።" አለው።

የሁዳው ደስታው ወደር አጣ ነገር ግን ድብቅ ሴራው እንዳይታወቅበት ደስታውን ደበቀው።

እረኛውም እንዲህ በማለት ንግግሩን ቀጠለ፦

"አንድ ጥያቄ አለኝ።

ባንተ የሰውነት አካል ውስጥ ድግምግሞሽ የለም?

ለምሳሌ፦ ሁለት እጅ

☞ሁለት አይን

☞ሁለት እግር

☞ሁለት ጆሮ.....

ታዲያ ሰውነትህ ቀለል እንዲልልህ አንድ አንዱን ለምን አትቆርጥም? ያው ድግምግሞሽ ነው እንጂ እኮ ምንም አይደለም"

ይሄን ሲለው የሁዳው ደነገጠ።ፊቱን አጨፍግጎ፦ "የእረኛዎቻቸው መልስ እንዲህ ከሆነ የዑለማኦቻቸው መልስ እንዴት ሊሆን ነው?" እያለ ከተማዋን ትቶ አለ

Send as a message
Share on my page
Share in the group