Translation is not possible.

  የአልቀሰም ብርጌድ መግለጫ

-የአልቀሳም ብርጌድ ቃል አቀባይ አቡ ዑበይዳህ በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ሰጥቷል።

“ሰላም ለነዚያ ለጌታቸው ካልሆነ በቀር ጀርባቸውን በማያጎንብሱት ላይ ይሁን!” በማለት የጀመረው ሙጃሂድ አቡ ዑበይዳህ፣“ጥቅምት 7 ቀን የጠላት ምሽጎች እንደ ሸረሪት ድር ሲፈርሱ እና አንድ ተዋጊያችን ሶስት የጠላት ታንኮችን ሲያወድም የአሏህ እርዳታ በአይናችን አይተናል!”በማለት አክሏል።

-“ጠላት በመኖሪያ ሕንፃዎችና በሆስፒታሎች ላይ ማነጣጠሩ ውርደትንና ሽንፈትን እንጂ ሌላን አያመላክትም” ያለው የሙጃሂዶቹ ቃል አቀባይ ሙጃሂድ አቡዑበይዳህ አያይዞም

የጠላት ወታደራዊ እና የስለላ የበላይነት አለ የሚባልበት ዘመን አብቅቷል!እናም የጽዮናዊት የሽንፈት ዘመን ጀምሯል!”በማለት በኦክቶበር 7 ላይ ያስመዘገቡት ድል ትልቅ ሞራል እንደፈጠረላቸውና እስከመጨረሻው ለመዋጋት መወሰናቸውን እወቁልን ብሏል!ጠላት ከጠበቀው በላይ ሽንፈትን እንዲቀምስ እናደርጋለን በማለትም ዝቷል የጀግኖቹ የሚድያ ሀላፊ ጀግናው ሙጃሂድ አቡ ዑበይዳህ!

ሐማስ ምክትል ሊቀመንበር ሳሌህ አል አሮሪ የፍልስጤም ተቃውሞ አሁንም የውጊያውን ሂደት እየተቆጣጠረ ነው እናም በዚህ ጦርነት ግቦቹን ከማሳካት ወደኋላ አይልም ብለዋል።

ለአረብ መሪዎች ጠንከር ያለ መልእክት ያስተላለፈው አቡ ዑበይዳህ“እኛ የእናንተን ታንክ፣አውሮፕላንና ወታደር አንፈልግም…ቀቅላችሁ ብሉት አይነት…ነገር ግን ቢያንስ ቢያንስ ትንሽዬ ሀሞት ካላችሁ የእርዳታ ተሽከርካሪዎችን እንዲታንቀሳቅሱ እንጠይቃለን!”በማለት በአረቦች ደዩስነትና ተወዳዳሪ የሌለው ፍርሐት በጣም እንደተበሳጩባቸውና እንዳፈሩባቸው በሚያመላክት ንግግር ክፉኛ ተችቷቸዋል!

“እየሩሳሌምን ነፃ ለማውጣት እና የሀገሪቱን ክብር ለማደስ በታሪካችን ወሳኝ ጦርነት ገጥሞናል!”ያለው የጀግኖቹ ቃል አቀባይ ጀግናው ሙጃሂድ አቡዑበይዳህ

የፍልስጤም እስረኞች ከየእስር ቤቱ ካልተፈቱ በስተቀር የጠላት እስረኞችን መፍታት አይታሰብም!ጠላት የፍልስጢን እስረኞችን በአንድ ጊዜ ለመፍታት ከፈለገ እኛም ተዘጋጅተናል”በማለት ሰብኣዊ እርዳታ እንድገባ በሚል የፅዮናዊት እስረኞችን መልቀቅ ትክክልና ተገቢ እንዳልሆነ በገደምዳሜው ጠቁሟል!

በጋዛ የሚገኘው የሃማስ እንቅስቃሴ ሃላፊ ያህያ ሲንዋር ለአል-አቅሳ ቲቪ እንደተናገሩት በተቃውሞው የተያዙ እስረኞችን በሙሉ ለመልቀቅ በወረራ የተያዙ እስረኞችን መፍታትን የሚያካትት የልውውጥ ስምምነት ለመደምደም ተዘጋጅተናል በማለት የአቡዑበይዳህን ንግግር ደግመዋል።

Send as a message
Share on my page
Share in the group