Translation is not possible.

🌹ሶብር🌹

👉ትግስት የዚህ አለም ሀብት የመጭው አለም ስኬት ናት። አላህ ለታጋሾች ትልቅ ስጦታን ሰጣቸዋ በገነትም አበሰራቸው።

وَلَنَبْلُوَنَّكُم بِشَيْءٍ مِّنَ الْخَوْفِ وَالْجُوعِ وَنَقْصٍ مِّنَ الْأَمْوَالِ وَالْأَنفُسِ وَالثَّمَرَاتِ ۗ وَبَشِّرِ الصَّابِرِينَ

ከፍርሃትና ከረኃብም በጥቂት ነገር፣ ከገንዘቦችና ከነፍሶችም፣ ከፍራፍሬዎችም በመቀነስ በእርግጥ እንሞክራችኋለን፡፡ ታጋሾችንም (በገነት) አብስር፡፡

'👉'ትግስት ከኢባዳዎች አንዱና ምንዳውም የላቀ ነው። አላህ ትእግስትን ከሶላት ጋር አብሮ በማቆራኘት ጠቅሶታል።

يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا اسْتَعِينُوا بِالصَّبْرِ وَالصَّلَاةِ ۚ إِنَّ اللَّهَ مَعَ الصَّابِرِينَ

እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በመታገስና በሶላት ተረዱ፡፡ አላህ (በእርዳታው) ከታጋሾች ጋር ነውና፡፡

الَّذِينَ إِذَا ذُكِرَ اللَّهُ وَجِلَتْ قُلُوبُهُمْ وَالصَّابِرِينَ عَلَىٰ مَا أَصَابَهُمْ وَالْمُقِيمِي الصَّلَاةِ وَمِمَّا رَزَقْنَاهُمْ يُنفِقُونَ

እነዚያን አላህ በተወሳ ጊዜ ልቦቻቸው የሚጨነቁትን፣ በደረሰባቸውም (መከራ) ላይ ታጋሾችን፣ ሶላትንም አስተካክለው ሰጋጆችን፣ ከሰጠናቸውም ሲሳይ የሚለግሱትን (አብስር)፡፡

'👉'ሳትፈተንና መከራን ሳትቀምስ ጀነትን የምታገኝ መሰለህን? አስታውስ! ጀነት ለነዚያ መከራና ችግር ባጋጠማቸው ጊዜ እንዲህ ለሚሉት ናት፦

👉''ብልህ ሰው ከችግርና መከራ ትምህርት ይወስዳል፣ ነገሮች ቢከብዱም ጌታውን  ያመሰግናል።

👉ታላቁ የትዕግስት መምህር ነብያችን ሱለላሁ አለይሂ ወሰለም ከፍ ባለ ድምፅ እዲህ ነበር ያሉት፦ "አዋጅ! የአላህ ሸቀጥ እጅግ ውድ ናት፣ የአላህ ሸቀጥ እርሷ ጀነት ናት። "

👉*እናም ችግርና መከራ ቢደራረብብህ አትዘን ተስፋ አትቁረጥም.... አላህ ምን እዳዘጋጀልህ አታውቅምና ታጋሽና አመስጋኝም ሁን

🌹وَلَسَوْفَ يُعْطِيكَ رَبُّكَ فَتَرْضَىٰ 🌹

👉ጌታህም ወደ ፊት (ብዙን ስጦታ) በእርግጥ ይሰጥሃል፡፡ ትደሰታለህም፡፡

'' አላህ ከታጋሾች ጋር መሆኑን አትርሳ።

إِنَّ اللَّهَ مَعَ الصَّابِرِينَ

👉 አላህ (በእርዳታው) ከታጋሾች ጋር ነውና፡፡

Send as a message
Share on my page
Share in the group