7 уйӑх Куҫарас
Çĕнĕ çулахне йывăçлăх

መሰረታዊ መርሆዎችና መስፈርቶች

እነዚያ እነሱ እውቀት የሚያዝባቸው ዑለማዖች ምን አይነት መስፈርት ማሟላት አለባቸው?

እውቀት የሚወሰድባቸው እና እነሱን የምንከተላቸው ኡለማዖች እነሱ ሐርብ አልከርማኒ ኢዕቲቃዱ ላይ እንዳለው ነው።

እነሱ እውቅ የሆኑ አዒማዎች ነበሩ፣ታማኞች፣የእውነተኝነትና የአደራ ባለቤቶች ነበሩ፣በነሱ መመራት አለ፤ከነሱ እውቀት ይያዛል።

የቢድዓ፣፣የልዩነት፣የመዘላበድ(የመቀላቀል) ባለቤቶች አልነበሩም።

በእውቀታቸው የሚሰሩ የሆኑ ኡለማዖች እና አህለ ሱናዎች ዘንድ በነሱ መከተል ባለቤቶች የሆኑ ኡለማዖች ዘንድ የድርሳናት ብዛት የመሸምደድ፣የዘገባዎች፣የእውቅና(ኢጃዛ መቀበል፣የአጫጭር ኪታቦች፣የግጥምች ብዛት መስፈርት አይደለም።ቁርዓንና ሀዲስን የዚች ኡማ ቀደምቶች የነበሩበትን መንገድ መከተል ነው መስፈርቱ።ይህም በ الله መገጠምና በእውቀት መሻት ቁርዓንና ሀዲስን ሰለፎች የነበሩበትን መንገድ በእምነትና በ ሸሪዓዎ ድንጋጌዎች ዱንያዊ በሆኑ ጉዳዮች መከተል ነው።

ኢብራሂም ቢን ኸዋስ እንዲህ ይላል፦እውቀት በዘገባ ብዛት አይደለም።ዒልም ማለት እውቀትን ለተከተለና ጥቅም ላይ ላዋለው ነው።ሱናን የተከተለ ነው አሊም ማለት ትንሽ እውቀት ቢኖረውም።

ሲየር ሰለፍ አስሷሊሂን 3/1325

ቀዋሙ አስሱና አልአስበሃኒ "አልሁጃ ፊ በያኒል መሐጃ" ላይ እንዲህ ይላል፦አህሉ ሱናዎች እንዲህ ይላሉ፦ኢልም በዘገባዎች ብዛት አይደለም።ዒልም ማለት እሱን መከተልና በሱ መጠቀም ነው።በዳጋጎቹና በታብዕዮች ይመራል።ትንሽ ዒልም ቢሆንም።ሱሃቦችን እና ታብዕዮችን የተቃረነ #ጠማማ ነው።ብዙ እውቀት ቢኖረውም።

በርበሃሪ الله ይዘንለትና እንዲህ ይላል፦እወቅ እውቀት የዘገባና የኪታብ ክምችት አይደለም።አዋቂ ማለትማ ቁርዓንና ሀዲስን የተከተለ ነው።ትንሽ እውቀትና ኪታብ ቢኖረው።ቁርዓንና ሀዲስን የተቃረነ #የቢድዓ_ባለቤት ነው።ብዙ ዘገባና ኪታብ ቢኖረውም።

ጦበቃቱል ሀናቢላ 2/30

ሸርሁ ሱና(144 ቁ) ላይ ደግሞ እንዲህ ይላል፦የነፍህን ነገር አደራህን,ፈለግን በመከተል የፈለግ ባለቤቶችንም በመከተል አደራህን በጭፍን በመከተልም ላይ,ዲን ማለት በጭፍን መከተል ነው–ማለትም ነብዩን እና የሳቸውን ባልደረቦች መከተል ነው።ከኛ በፊት የነበሩት ሸፋፋነው አልተውንም፤እነሱን ተከተል ታርፋለህ(ትረጋጋለህ)፣ፈለግን እና የፈለግን ባለቤቶችን አትተላለፍ።

ታላቁ ኢማም ኢስሐቅ ቢን ረሓወይህ الله ይዘንለትና እንዲህ ይላል፦እኛማ የመከተልና በጭፍን የመከተል ባለቤቶች ብቻ ነን እነዚህም የምንከተላቸው الله ይዘንላቸውና አዒማዎችና ቀደምቶች ናቸው። በ الله ኪታብ በነብዩ ሱና የሌለን አዲስ ፈጠራን አናስገኝም። ኢማሞች ያላሉትን ጭምር አዲስ ፈጠራን አንፈጥርም።

አስ–ሱናህ ሊልኸላል 2179

ላለካዒ ዘንድ (

ኢብራሂም ሀርቢ (እውቀት ከታላላቆቻቸው እስከመጣላቸው ድረስ በኸይር ላይ ከመሆን አይወገዱም) በሚል በዚህ ንግግር ላይ ተዕሊቅ ሲያደርግ ይህ ማለት ትንሽ ሆኖ የነብዩን የሱሃቦችን እና የታብዕዮችን ንግግር የተከተል ትልቅ ነው።ትልቅ አንጋፋ የአቢ ሀኒፋን ንግግር ከያዘና የነብዩን ሱና ከተው እሱ ነው ትንሽ ማለት።

አቡ ነስር አስሲጅዚ الله ይዘንለትና እንዲህ ይላል፦የሰለፎችን ፈለግ የሚከተልን ማስቀደምና ማክበር ግዴታ ነው።በእድሜ ትንሽ ቢሆንም የድርሻ ባለቤት ባይሆንም።አሰርን የተፃረረ እሱን መራቅ ግዴታ ነው።ትልቅ(ጠና ያለ) የትልቅ ዝና ባለቤትም ቢሆንም እንኳ።

ሪሳለቱ ኢላ አህሊ ዘቢይድ (ገፅ 340)

ፈድል ቢን ዘያድ እንዲህ ይላል፦አቡ አብዲላህን–አህመድ ቢን ሐንበልን–ስለ ከራቢሲና ይፋ ስላደረገው ነገር ጠየቅኩት ፊቱን አዞረብኝ ከዚያም እንዲህ አለኝ የነሱ ፈተና የመጣው ከነዚህ ካስቀመጧቸው መፃህፍት ነው።የነብዩን እና የባልደረቦቹን ፋና ተው።ወደነዚህ መፃህፍቶች ፊታቸውን አዞሩ።

እኔም (አዲል አልሃምዳን እላለሁ፦

አብዛኛዎቹ ከኋላ ዘግይተው የመጡት ይህን መስፈርት ብኩን አደረጉትና በቁቡርዮች,በጀሕምዮች,በሙዓጢላዎች የአህለ ሱናንም እምነትና አካሄድን በተቃረኑት ላይ በተለያዩ የሙገሳና ውዳሴ በዲን ላይ ኢማማነትንም ተጠቀሙ።ወደ ኢልም የተሰየሙ በመሆናቸው ብቻ ወይም በኢባዳ ስለታወቁ ብቻ (እነዚህን አዒማነትን ለነሱ ሰጡ) ይህም የሱና ሊቃውንት የነበሩበትን ይፃረራል።

ኪታቡ አሽሸሪዓህ ሊል አጁሪ (ገፅ 26–27)

ተህቂቅ አቡ አብዲላህ አድል ቢን አብዲላህ አልሐምዳን

#quran #islam #gaza

image
Хыпар пек ярас
Ман тетелӗ питра пайлас
Ушкӑнта пайлас