Translation is not possible.

የጁምዓ ቀን ትሩፋቶች

فضلُ يوم الجمعةِ

""""""""""""""""""""""

1⃣ قال رسول الله ﷺ :

(أفضلُ الأَيَّامِ عندَ اللهِ يومُ الجمعةِ)

አቡ ሁረይራ [ረዲየላሁ አንሁ] እንዳስተላለፉልን

የአላህ መልእክተኛ [ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም] «አላህ ዘንድ በላጩ ቀን የጁምዓ እለት ነው።» ብለዋል።

📚صححه الألباني في

السلسلة الصحيحة - رقم: (1502)

صحيح الجامع - رقم: (1098)

2⃣ قال رسول الله ﷺ :

(( أفضلُ الصلواتِ عند اللهِ صلاةُ الصبحِ يومَ الجمعةِ في جماعةٍ ))

አብደላህ ኢብኑ ዑመር [ረዲየላሁ አንሁማ] ባስተላለፉልን መሰረት

የአላህ መልእክተኛ [ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም] «አላህ ዘንድ ከሰላቶች መካከል በላጭ የሆነው ሰላት የጁምዓ እለት በጀማዓ የተሰገደ የሱብሂ ሰላት ነው።» ብለዋል።

📚السلسلة الصحيحة -

الألباني صحيح - رقم: 1566

3⃣ قال رسول الله ﷺ :

(( أكثِروا الصَّلاةَ عليَّ يومَ الجمُعةِ و ليلةَ الجمُعةِ ، فمَن صلَّى عليَّ صلاةً صلَّى اللهُ عليهِ عَشرًا ))

አነስ ኢብኑ ማሊክ [ረዲየላሁ አንሁ] ባስተላለፉልን መሰረት

የአላህ መልእክተኛ [ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም] «ጁምዓ ቀንና ጁምዓ ምሽት በኔ ላይ ሰለዋትን አብዙ። በኔ ላይ አንዴ ሰለዋትን ያወረደ አላህ በሱ ላይ አስር ሰለዋትን ያወርድለታል።» ብለዋል።

📚صحيح الجامع

الألباني حسن - رقم: 1209

4⃣ قال رسول الله ﷺ :

(( ما مِن مسلمٍ يموتُ يومَ الجمعةِ أو ليلةَ الجمعةِ إلَّا وقاهُ اللَّهُ فِتنةَ القبرِ ))

አብደላህ ኢብኑ ዑመር [ረዲየላሁ አንሁማ] እንዳስተላለፉልን

የአላህ መልእክተኛ [ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም] «ከሙስሊሞች መካከል ማንኛውም ሰው በጁምዓ ቀን ወይም በጁምዓ ምሽት ከሞተ … አላህ ከቀብር ፊትና ሳይጠብቀው አይቀርም።» ብለዋል።

📚حسنه الألباني في صحيح الترمذي - رقم: (1074) ، تخريج مشكاة المصابيح - رقم: (1316) الألباني :إسناده حسن أو صحيح لغيره

5⃣ قال رسول الله ﷺ :

(( الصَّلاةُ الخمسُ والجمعةُ إلى الجمعةِ كفَّارةٌ لما بينَهنَّ ما لم تُغشَ الْكبائرُ ))

አቡ ሁረይራ [ረዲየላሁ አንሁ] እንዳስተላለፉልን

የአላህ መልእክተኛ [ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም] «አምስቱ የግዴታ ሰላቶችና ከጁምዓ እስከ ጁምዓ … ከባባድ ወንጀሎች ኖረው ካልጋረዱ በስተቀር በመካከላቸው የተፈፀሙትን ሌሎች ኃጢኣቶች ያብሳሉ።» ብለዋል።

📚صحيح مسلم - رقم: (233)

6⃣ وفي رواية اخرى :

(( الجمُعةُ إلى الجمُعةِ كفَّارةُ ما بينهما ما لم تُغْشَ الكبائرُ ))

አባሁረይራ [ረዲየላሁ አንሁ] እንዳስተላለፉልን

የአላህ መልእክተኛ [ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም] «ከጁምዓ እስከ ጁምዓ … ከባባድ ወንጀሎች ኖረው ካልጋረዱ በስተቀር በመካከላቸው ያሉትን ሌሎች ኃጢኣቶች ያብሳሉ።» ብለዋል።

📚الألباني - صحيح الجامع رقم: (3110)

7⃣ قال رسول الله ﷺ :

(( لا يُقيمَنَّ أحدُكم أخاه يومَ الجُمُعةِ . ثم لِيخالفَ إلى مقعدِه فيقعدُ فيه . ولكن يقولُ : أَفسِحُوا ))

አብደላህ ኢብኑ ዑመር [ረዲየላሁ አንሁማ] ባስተላለፉልን መሰረትም

የአላህ መልእክተኛ [ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም] «አንዳችሁም የጁምዓ እለት (መስጂድ ውስጥ) ወንድሙን ከተቀመጠበት አያስነሳው፤ ከዚያም ወንድሙ ከተነሳበት ቦታ እሱ ሊቀመጥ አይገባውምነ። ነገር ግን (ክፍተት ካለ) ሰፋሰፋ አድርጉ (ተጠጋግታችሁ ክፍት መቀመጫ ስጡን) ይበል።» ብለዋል።

📚صحيح مسلم - رقم: (2178)

8⃣ قال رسول الله ﷺ :

(( إذا راح أحدُكم إلى الجمعةِ فليغتسلْ ))

አብደላህ ኢብኑ ዑመር [ረዲየላሁ አንሁማ] እንዳስተላለፉልን

የአላህ መልእክተኛ [ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም] «አንዳችሁ ወደ ጁምዓ ሲሄድ ይታጠብ።» ብለዋል።

📚صحيح البخاري - رقم: (882)

9⃣ قال رسول الله ﷺ :

(( مَن قرأَ سورةَ الكَهفِ في يومِ الجمعةِ ؛ أضاءَ لهُ منَ النُّورِ ما بينَ الجُمعتَينِ ))

አቢ ሠዒድ አልኹድሪይ [ረዲየላሁ አንሁ] ባስተላለፉልን መሰረት

የአላህ መልእክተኛ [ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም] «የጁምዓ ቀን ሱረቱል ካህፍን ላነበበ ሰው በሁለቱ ጁምዓዎች መካከል (ያለውን ርቀት ያህል) ከብርሃን ያበራለታል።» ብለዋል።

📚حسنه الألباني في

تخريج مشكاة المصابيح - رقم:(2116)

🔟 وفي رواية اخرى :

(( من قرأ سورةَ الكهفِ ليلةَ الجمعةِ ، أضاء له من النورِ ما بينه وبين البيتِ العتيقِ ))

አቢ ሠዒድ አልኹድሪይ [ረዲየላሁ አንሁ] ባስተላለፉልን መሰረት

የአላህ መልእክተኛ [ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም] «የጁምዓ ቀን ሱረቱል ካህፍን ላነበበ ሰው በሱ እና በበይተል ዐቲቅ መካከል ያለውን ርቀት ያህል ከብርሃን ያበራለታል።» ብለዋል።

📚صححه الألباني في

صحيح الترغيب -رقم: (736)

የኢስላም ምሁራን እንዳሉት… ብርሃን ማለት በዱንያ ላይ ሳለ ከወንጀሎች የሚጠበቅበት፣ መልካም ስራዎች ላይ የሚተጋበት እውቀት፣ ኢማን ይጨምርለታል። ወይም ነገ የቂያም ቀን ከእግሩ ስር ብርሃን ይሆንለታል በማለት አስተያየት ሰጥተዋል።

Umer musa

▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴▴

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group