Наган дахаан йохтахам.

የሄዝቦላ መሪ ከፍልስጤም ታጣቂ ቡድኖች አመራሮች ጋር ድል በማድረግ ጉዳይ መከረ

የሊባኖሱ የሄዝቦላ መሪ ከፍልስጤም ከፍተኛ አመራሮች ጋር ተገናኝቶ "ድል በማድረግ" ጉዳይ ተወያይቷል።

መሪው ከፍልስጤም ታጣቂ ቡድኖች ጋር መገናኘቱን ሮይተርስ የሄዝባላውን አል-ማናር ቴሌቪዥን ጠቅሶ ዘግቧል።

እንደዘገባው ከሆነ የፍልስጤም ታጣቂ ቡድኖቹ ሀማስ እና እስላማዊ ጅሃድ ከሄዝቦላ መሪ ጋር በተገናኙበት ወቅት በጋዛ ያለውን ትግል በድል ለማጠናቀቅ ጥምረታቸው ምን መሆን እንዳለበት ተወያይተዋል።

@Palestine_quds

ስብሰባውን የሄዝቦላው ሰይድ ሀሰን ነስረላህ፣ የሀማስ ምክትል ኃላፊ ሳላህ አል አሮሪ እና የእስላማዊ ጅሃድ ኃላፊ ዛይድ አል ናቅሃላ ማካሄዳቸውን አል ማናር በዘገባው ገልጿል።

"በስብሰባው...በአለም አቀፍ ደረጃ የተያዘውን አቋም በመገምገም፣ ትግሉ ምን መምሰል አለበት" በሚለው ጉዳይ ምክክር መደረጉን ይኸው ሚዲያ ዘግቧል።

በሊባኖስ፣ ሶሪያ እና በየመን ያሉ ታጣቂዎች እንዲሁም ኢራን ከእስራኤል ጋር ለገጠመው ሀማስ አጋርነታቸውን አሳይተዋል።

@Palestine_quds

Send as a message
Share on my page
Share in the group