Translation is not possible.
✏️የነቢያችን_ሰለሏሁ_ዐለይሂ_ወሰለም_የአመጋገብ_ሱና
 
✏️➊➭ ነቢያችን ከምግብ በፊት ይታጠቡ ነበር። የሚበሉትም ከፊታቸው ነበር
 
✏️➋➭ ነቢያችን ተደግፈው በልተው አያውቁም። ለምግብ ሲቀመጡ ወይ ተሸሁድ ላይ አይነት፣ ወይም እንዲሁ ተቀምጠው አንድ እግራቸውን ጉልበት ደረታቸው ላይ በማቀፍ ወይ ደግሞ ቁጢጥ በማለት ነበር።
 
✏️➌➭ ነቢዩ ምግብ ሲጀምሩ ቢስሚላህ በማለት ነው።
 
✏️➍ ➭ነቢያችን ምግቡን ካልወደዱት ስለምግቡ ምንም ሳይናገሩ መመገብ ይተው ነበር።
 
✏️➭ የማያውቁት ምግብ ከገጠማቸው አስቀድመው ስለምግቡ ይጠይቁ ነበር።
 
✏️➏ ➭ነቢያችን ምግባቸውን አሽትተው አያውቁም። ጥሩ ያለሆነ ልምድ እንደሆነም ይቆጥሩታል።
 
✏️➐ ➭በጣም የሞቀ ምግብ አይመገቡም ያቀዘቅዙት ነበር። «አላሁ ተዐላ እሳት አይመግበንም» ይሉ ነበር። በጣም የሞቀ ምግብ ውስጥ በረካ የለውም ብለዋል።
 
✏️➑➭ ነበዩ ምግብም ሆነ መጠጥ ላይ ተንፍሰው አያውቁም። መጠጥን በትንፋሽ ማቀዝቀዝ አይወዱም ነበር።
 
✏️➒ ➭ነቢዩ ሀብታሞች ቤት እንደሚሆነው በብዙ ሳህን የሚቀርብ ምግብ አይወዱም ነበር።
 
✏️➓ ➭በአብዛኛው ነቢዩ ሲመገቡ በሶስት ጣታቸው (አውራ፣ ጠቋሚና መሐል ጣታቸውን) በመጠቀም ሲሆን ምግቡ ቀጠን ያለ ከሆነ ቀለበት ጣታቸውን ይጨምሩ ነበር።
 
✏️➊➊➭ አንድ አይነት ምግብ ከቀረበላቸው ከፊታቸው ይመገባሉ የተለያየ አይነት ከሆነ ግን ከሌላ ቦታ ከመመገብ አይቆጠቡም ነበር።
 
✏️➊➋ ➭ነቢዩ ከሰው ጋር እየበሉ ከሆነ የሚነሱት በመጨረሻ ነበር። ቀስ ብለው የሚመገቡ ሰዎችን ላለማሳፈር።
 
✏️➊➌➭ ሲጨርሱ ጣታጫውን በአፋቸው ያፀዱ ነበር።
 
✏️➊➍➭ ነቢዩ ተመግበው ሲጨርሱ እንዲህ ይሉ ነበር «የምንበላውና የምንጠጣውን የሰጠኸን፣ ሙስሊምም ያደረግኸን አምላክ ምስጋና ይገባህ!» ይሉ ነበር።
 
✏️➊➎➭ ነቢዩ ምግብ ለተሰባሰቡ ሰዎች የሚያከፋፍሉ ከሆነ በቀኝ ይጀምሩ ነበር። በግራ መጀመር ከፈለጉ በቀኝ ያለውን ያስፈቅዱ ነበር።
 
✏️➊➏ ➭ነቢያችን ስጋ ወደ ቤት ሲያመጡ ለጎረቤት እንዲበቃ ተደርጎ እንዲሰራ ያደርጉ ነበር።
 
✏️➊➐➭ ነቢዩ ሀለዋ፣ ማር፣ ኮምጣቴ፣ ተምር፣ ሀብሀብ፣ ኪያር እና ዝኩኒ ይወዱ ነበር።
Send as a message
Share on my page
Share in the group