Translation is not possible.

ሩዋንዳ 16 ቶን እርዳታ ወደ ጋዛ ላከች‼️

የሩዋንዳ መንግስት በጋዛ ለሚገኙ የፍልስጤም ህዝብ ሰብአዊ እርዳታ ልኳል። የመንግስት ምክትል ቃል አቀባይ አላይን ሙኩራሊንዳ እንደተናገሩት ድጋፉ ለጆርዳን ሃሽሚት በጎ አድራጎት ድርጅት የተላከ ሲሆን በዮርዳኖስ ዋና ከተማ አማን ደርሷል።

ሙኩራሊንዳ “እየተካሄደ ያለውን ዓለም አቀፍ የነፍስ አድን ጥረት ለመደገፍ ” ያለመ እንቅስቃሴ መሆኑን ገልፀዋል። ልገሳው 16 ቶን የምግብ እቃዎች፣ መድሀኒቶች እና የህክምና አቅርቦቶች ያካተተ ሲሆን "ሩዋንዳ የንፁሀን ዜጎችን ህይወት ለመጠበቅ መረጋጋት እንደሚያስፈልግ ገልፃለች።

ሩዋንዳ ከእስራኤል ጋር የጠበቀ ግንኙነት ካላቸው የአፍሪካ ሀገራት መካከል አንዷ ነች። የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ በ2016 ሩዋንዳ መጎብኘታቸው ይታወሳል። በሩዋንዳ እ.ኤ.አ. በ1994 በደረሰው የዘር ማጥፋት ወንጀል ሰለባ ለሆኑ ሰዎች መታሰቢያ ስፍራብ ከጎበኙ በኋላ ኔታንያሁ ባሰፈሩት የፁሁፍ መልዕክት ፍ ላይ “ከህዝባችን ጭፍጨፋ ጋር ተመሳሳይነት አለው” ሲሉ አክለዋል።

እኤአ በ1994 ከ800 ሺ የሚበልጡ የቱትሲ ጎሣዎች መጨፍጨፋቸው ይታወሳል።በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት ስድስት ሚሊዮን አይሁዳውያን በሆሎኮስት ተገድለዋል።

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group