Translation is not possible.

አላህ እንዲህ ብሏል፦

“...ስለ ስህተትህም ለምእመናንም ምሕረትን ለምን፡፡...”

📖 (ሙሐመድ፡ 19)

ኢብራሂም (ዐ.ሰ) እንዲህ ሲሉ መማጸናቸው ተገልጿል፦

«ጌታችን ሆይ! ለእኔም ለወላጆቼም ለምእመናንም ሁሉ ምርመራ በሚደረግበት ቀን ማር፡፡»

📖 (ኢብራሂም፡ 41)

አቡ ደርዳእ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) እንዲህ ይሉ ነበር፦

“አንድ ሙስሊም ከአጠገቡ ለሌለ ወንድሙ የሚያደርገው ዱዓ ተቀባይነት አለው። ከራሱ ላይ ለዚሁ ተግባር የተሰየመ መላኢካ አለ። ሰውየው ለወንድሙ በበጎ ነገር ዱዓ ባደረገለት ቁጥር መላኢካው፦ አሚን፤ ለርሱ የጠየቅለት ነገር ላንተም ይስጥህ፤ ይላል።”

📚 ሙስሊም ዝግበውታል

📚ሪያዱ አስ-ሷሊሒን [1495]

📨📨📨 ከሐዲሡ የምንማረው ቁምነገር 📨📨📨

(☞) ሙስሊም ለራሱም ለወንድሙም ዱዓ ማድረግ ይወደዳል። ይህንን በማድረጉ ዱዓው ተቀባይነት ያገኛል። ለወንድሙ የጠየቀውንም በጎ ነገር እርሱ ራሱ ይጎናጸፋል።

🔀 ሼር ማድረግ አይርሱ

የበለጠ ለማወቅ

ሶሒህ ሐዲሶች በዐማርኛ የሚለቀቅበት ዓለም ዐቀፍ ግሩፕ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group