Translation is not possible.

ስቃዬን የሰማ መበደሌን ያየ

ጨቋኜ እንዳይከፋው አለፈ እንዳላየ

ጎኔን ሰው ሲርበው ጠላቴ እያደባ

እኔ አውቅልህ አለኝ ደም እንባ እያስነባ።

የሚያርፍብኝ በትር ሊሰብረኝ መች ቻለ

ብቸኝነቱ ነው ውስጤን ያቆሰለ

ዙርያዬ ቢከበብ በአድማቂና አጃቢ

ካለ ወንድም አይሆን ወንድም ስጠኝ ረቢ።

ያ ወዱድ

ያ ወዱድ!

ትላንት ያሳደግኋት ያቺ ትንሽ ግልገል

አንዴ ብትረግጠኝ ተሰበርኹ እንደ ገል

እንኳንስ የሩቁ የቅርቤም አልሆነኝ

እኔ አቅም የለኝም ጌታዬ አንተው ሁነኝ።

[ አብዱልሀኪም ሰፋ ]

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group