Çeviri imkansız.

📌|በአላህ ላይ ያለ እውቀት መናገር

ዛሬ ላይ ብዙ ሰዎች በአላህ ዲን ላይ በድፍረት ሲከራከሩ ሲሞግቱ ይውላሉ፤በቁርኣን ተፍሲር ላይ የሰለፎችን ተፍሲር ሳይማሩ በሰሟቸው ዳዕዋ ብቻ ሰፊውን እስልምና በጠባቡ ጭንቅላታቸው ገድበው ከቀደምት አኢማዎች የተገኙ ግልፅ ተፍሲሮችን ሲያስተባብሉ፤ሱንናውን ቢድዓ ነው ቢድዓውን ሱንና ነወረ ሲሉ ትንሽ እንኳን አያፍሩም።አላሁልሙስተዐን

ወንድሞች በአላህ ዲን ላይ ያለ እውቀት መናገር ታላቁ ወንጀል ሲሆን ከሽርክ የሚተናነስ አይደለም።

﴿قُلۡ إِنَّمَا حَرَّمَ رَبِّیَ ٱلۡفَوَ ٰ⁠حِشَ مَا ظَهَرَ مِنۡهَا وَمَا بَطَنَ وَٱلۡإِثۡمَ وَٱلۡبَغۡیَ بِغَیۡرِ ٱلۡحَقِّ وَأَن تُشۡرِكُوا۟ بِٱللَّهِ مَا لَمۡ یُنَزِّلۡ بِهِۦ سُلۡطَـٰنࣰا وَأَن تَقُولُوا۟ عَلَى ٱللَّهِ مَا لَا تَعۡلَمُونَ﴾ [الأعراف ٣٣]

አሏህ እንዲህ ብሏል《"33" «ጌታዬ እርም ያደረገው መጥፎ ሥራዎችን፣ ከርሷ የተገለጸውንና የተደበቀውን ኃጢኣትንም፣ ያላግባብ መበደልንም፣ በርሱም ማስረጃ ያላወረደበትን (ጣዖት) በአላህ ማጋራታችሁን፣ በአላህም ላይ የማታውቁትን መናገራችሁን ብቻ ነው» በላቸው፡》

✍️ ‏قال القاسم بن محمد : «لَأن يعيش الرجل جاهلًا، خيرٌ له من أن يقول على الله ما لا يعلم» 📙 الجامع في العقائد | لـ آل حمدان ٤٩٤/١

🍂ኢማም ቃሲም ቢን ሙሐመድ እንዲህ ብለዋል «አንድ ሰው ያለ እውቀቱ በአላህ ላይ ከሚናገር ህይወቱን ሙሉ ጃሂል ሆኖ ቢቀር ይሻለዋል።» 📙አል-ጃሚዕ ፊ አል-ዐቃኢድ 1/494

#islam

Mesaj olarak gönder
Sayfamda paylaş
Grupta paylaş